
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 19/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮ-ቴሌኮም ከመልቲ ቾይዝ ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር ዲ ኤስ ቲቪ ስትሪም ጥቅል የተባለ አገልግሎት ይፋ አድርጓል።
ስምምነቱ ቀልጣፋ ፈጣንና በየትኛውም ጊዜና ቦታ የላቀ ጥራት ያላቸውን ይዘቶች በተለያዩ ስማርት ስልኮች ማግኘት የሚያስችል ነው።
ጥቅሉ ከድምጽና ኢንተርኔት ግንኙነት በተጨማሪ የተለያዩ ተወዳጅ የስፖርት ቻናሎችን ጥራታቸውን በጠበቀ መልኩ ማየት የሚያስችል መሆኑም ተገልጿል፡፡

እንዲሁም ሀገርኛ ይዘቶችን፣ ዓለም አቀፍ ፊልሞችን፣ ዶክመንተሪዎችንና የተለያዩ ሾዎችን መመልከት የሚያስችል መሆኑ ተመላክቷል።
የኢትዮ-ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ በዚህ ወቅት ትብብሩ ኢትዮ ቴሌኮም ሁሉንም አገልግሎቶች ዲጂታላይዝ ለማድረግ እየተጓዘበት ያለውን ርቀት የሚያሳይ ነው ብለዋል።
የመልቲ ቾይስ ኢትዮጵያ ዋና ዳይሬክተር ገሊላ ገብረሚካኤል በበኩላቸው ዲኤስቲቪ ስትሪም ጥቅል አገልግሎት የተለያዩ አማራጮችን የያዘ ጎጆ ቤተሰብ፣ ሜዳ ፕላስና ፕሪሚየምን ያካተተ መሆኑን ተናግረዋል።
ይህም ደንበኞች የሚፈልጉትን አገልግሎት መርጠው እንዲጠቀሙ የሚያስችል መሆኑንም ገልጸዋል።
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026
ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...
Apr 3, 2026
ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...
Mar 31, 2026
ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...
Mar 26, 2026