የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የኢትዮጵያ የዲጂታል መሰረተ ልማት ግንባታ ለአፍሪካ ሀገራት ትምህርት ይሆናል

Apr 3, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ሀገራት ትምህርት የሚሆን የዲጂታል ኢኮኖሚና መሰረተ ልማት እየገነባች መሆኑን በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን የፈጠራና ቴክኖሎጂ ክፍል ኃላፊ ማክታር ሳክ(ዶ/ር) ገልጸዋል።

ኃላፊው ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የአፍሪካ ሀገራት ጠንካራ የዲጂታል ፖሊሲ በመዘርጋት የከተማና ገጠር የቴክኖሎጂ ትስስርን በማስፋፋት በቁርጠኝነት መስራት ይጠበቅባቸዋል።

ኢትዮጵያ ለዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ በሰጠችው ትኩረት በስራ ዕድል ፈጠራና በኢንቨስትመንት ፍሰት እመርታዊ ለውጥ እያስመዘገበች እንደምትገኝ ገልጸዋል።

መንግሥት ለዲጂታላይዜሽን በሰጠው ትኩረት የኢንተርኔት መሰረተ ልማት ተደራሽነት በሀገሪቱ በእጅጉ መስፋፋቱን አድንቀዋል።

ጠንካራ የኢንፎርሜሽን ኮሙኒኬሽን ቴክኖሎጂ የአሰራር ማዕቀፍ በማዘጋጀት የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ቀጣና ስምምነትን ማቀላጠፍ እንደሚያስፈልግም አጽንኦት ሰጥተዋል።

የበይነ መረብ ግንኙነት ዕድገትም ለአህጉሪቱ ነፃ ንግድ ቀጣና ስምምነት መሳካት ወሳኝ በመሆኑ ለአፍሪካውያን ተመጣጣኝ አገልግሎት ማቅረብ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

ከዚህ አኳያ ኢትዮጵያ በዲጂታል መሰረተ ልማትና ኢኮኖሚ ግንባታ ለአፍሪካውያን ትምህርት የሚሆን ስኬት እያስመዘገበች ነው ብለዋል።


የቴክኖሎጂ ንግድ ልማትና ግብይት ባለሙያ የሆኑት ሰርጌይ ጋስፓርያን በበኩላቸው፤ የቴክኖሎጂ መሰረተ ልማት የሀገር ውስጥ ገቢ የመሰብሰብ አቅምን ለማሳደግ ወሳኝ ነው ብለዋል።

ዲጂታላይዜሽን የፋይናንስ አስተዳደርንና የታክስ የመሰብሰብ ሂደትን በማቀላጠፍ ግልጽነት ያለው የገቢና ወጪ ሥርዓት ለመፍጠር ጉልህ ጠቀሜታ እንዳለው ገልጸዋል።

ኢትዮጵያም የአምስት ዓመታት የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ስትራቴጂ በመቅረጽ ባለፉት ዓመታት ያከናወነቻቸው ተግባራት የሚደነቁ ናቸው ብለዋል።

በቀጣይም ከዓለም አቀፍ የቴክኖሎጂ ምርትና አገልግሎት ሰጪዎች ጋር በመተባበር የዕውቀትና ክህሎት ሽግግር ላይ በትኩረት መስራት እንደሚገባም አንስተዋል።

ኢትዮጵያ የመንግስትን የመፈጸም አቅም በማሳደግ ጠንካራ የኢኮኖሚ ዕድገት በመፍጠር አስደናቂ የልማት እንቅስቃሴ እያደረገች መሆኗንም ጠቅሰዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026