የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በክልሉ ሠላምን በማፅናት ዘላቂ ልማት ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው

Mar 17, 2025

IDOPRESS

ሚዛን አማን፣መጋቢት 7/2017 (ኢዜአ)፡-በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ሠላምን በማፅናት ዘላቂ ልማት ማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር) ገለጹ።


በሠላምና ልማት ዙሪያ የሚያተኩር የምክክር መድረክ በሚዛን አማን ከተማ እየተካሄደ ነው።


ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር እየተካሄደ ባለው መድረክ ላይ የተገኙት ርዕሰ መስተዳደሩ እንዳመለከቱት፥ ባለፉት ሦስት ዓመታት ተኩል በክልሉ የሠላም ግንባታ፣የልማትና፣የመልካም አስተዳደር ሥራዎች ሲከናወኑ ቆየተዋል።


በዚህም ውጤት መገኘቱን ገልጸው፥በተለይ በምዕራብ ኦሞ ዞን ከፀጥታ ጋር ተያይዞ የነበረው ችግር እየተፈታ ለልማት ምቹ ሁኔታ መፍጠር መቻሉን ተናግረዋል።


ይህን አጠናክሮ በማስቀጠልና ሠላምን በማፅናት ዘላቂ ልማት ማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።


በክልል በተለይ የዞኑን ሠላም በማስጠበቅ ልማትን ለማጠናከር በሚቻልበት ላይ ዛሬ እየመከረ ያለው መድረክ በተመሳሳይ እስከታችኛው መዋቅር ድረስ እንደሚቀጥል ጠቁመዋል።


በአማን ከተማ እየተካሄደ ባለው መድረክ ላይ የክልሉና የምዕራብ ኦሞ ዞን አመራር አባላት እንዲሁም ሌሎችም ባለድርሻ አካላት በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026