
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 7/2017(ኢዜአ)፡- በአዲስ አበባ ከተማ 154ሺህ 923 ነዋሪዎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ የከተማ ልማታዊ ሴፍትኔት እና የስራ ፕሮጀክት ተጠቃሚዎች ፕሮግራም በይፋ ተጀምሯል።
የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ እና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ሀላፊ ጃንጥራር አባይ ፕሮግራሙን በከተማ ደረጃ በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 በይፋ ባስጀመሩበት ወቅት እንደገለጹት የከተማ ልማት ሴፍትኔት ፕሮግራሙ ለሶስተኛ ዙር በከተማው እንደሚካሄድ ተናግረዋል።

ከዚህ በፊት በተካሄዱ ሁለት ዙር የልማት ሴፍትኔት ፕሮግራሞች ነዋሪዎችን ተጠቃሚ ያደረጉ ውጤታማ ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸዋል።
ዛሬ በተጀመረው ሶስተኛ ዙር የከተማ ልማታዊ ሴፍትኔት እና የስራ ፕሮጀክት ላይ የሚሳተፋ ነዋሪዎች ውጤታማ እንዲሆኑ የተጠናከረ ድጋፍና ክትትል እንደሚደረግ አስታውቀዋል።
በአጠቃላይ በፕሮግራሙ 154ሺህ 923 ለተለያዩ ችግሮች ተጋላጭ የሆኑ የማህበረሰብ ክፍሎች ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ተመላክቷል።
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026
ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...
Apr 3, 2026
ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...
Mar 31, 2026
ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...
Mar 26, 2026