የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የኤሌክትሪክና ታዳሽ ኃይል ተጠቃሚ ተሽከርካሪዎችን በማላመድ አረንጓዴ ልማትን መገንባት ይገባል

Mar 12, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤መጋቢት 3/2017(ኢዜአ)፦የኤሌክትሪክና ታዳሽ ኃይል ተጠቃሚ ተሽከርካሪዎችን በማላመድ አረንጓዴ ልማትን ለመገንባት ባለድርሻ አካላት በቅንጅት ሊሰሩ እንደሚገባ የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር አለሙ ስሜ(ዶ/ር) ገለፁ።


በኤሌክትሪክና ታዳሽ ኃይል ተጠቃሚ ተሽከርካሪዎች ማስፈፀሚያ ረቂቅ ስትራቴጂ ላይ ውይይት እየተካሄደ ይገኛል።


ስትራቴጂውን የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር ከኢንዱስትሪ ሚኒስቴር በጋራ እንዳዘጋጁት በመድረኩ ተገልጿል፡፡


በውይይቱ የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ፣ የትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ሚኒስትር አለሙ ስሜ (ዶ/ር)፣ ሚኒስትር ዴኤታዎችና ከፍተኛ የመንግስት ኃላፊዎች ተገኝተዋል።


በዚሁ ወቅት የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር አለሙ ስሜ (ዶ/ር) ኢትዮጵያ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ኢኮኖሚ ለመገንባት በቁርጠኝነት እየሰራች እንደምትገኝ ተናግረዋል።


የትራንስፖርት ዘርፉ አረንጓዴ ኢኮኖሚ ለመገንባት ወሳኝ መሆኑን ጠቁመው ለስኬታማነቱ ዘርፉን የታዳሽ ኃይል ተጠቃሚ ማድረግ አስፈላጊ እንደሆነም ጠቅሰዋል።


ታዳሽ ሃይል የአየር ብክለትን ከመቀነስ ባለፈ ለነዳጅ የሚወጣውን ከፍተኛ ወጪ ለሌሎች መሰረተ ልማቶች ግንባታ ለማዋል ያስችላል ነው ያሉት።


ከተሞችን ፅዱና ስማርት ለማድረግ የጎላ ሚና እንዳለው ጠቅሰው፥ ለዚህ ደግሞ የኤሌክትሪክና ታዳሽ ኃይል ተጠቃሚ ተሽከርካሪዎችን ማስፋፋት እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡


ይህን ለማሳካት የሁሉንም ቅንጅት የሚጠይቅ ነው ብለዋል።


መድረኩ የኤሌክትሪክና ታዳሽ ኃይል ተጠቃሚ ተሽከርካሪዎች ማስፈፀሚያ ረቂቅ ስትራቴጂ ላይ ከመወያየት ባለፈ ወደ ተጨባጭ ስራ ለመግባት የሚያስችል መሆኑንም አስታውቀዋል።


በዚህም ታዳሽ ኃይል የሚጠቀሙ ተሽከርካሪዎችን በስፋት ስራ ላይ ለማዋል የሚመለከታቸው አካላት በቅንጅት እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026