
አዲስ አበባ፤መጋቢት 2/2017 (ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት እና የአዲስ አበባ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ በጥራት ማረጋገጫ ዘርፍ በትብብር መስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ስምምነት ዛሬ ተፈራርመዋል።
ስምምነቱን የተፈራረሙት የድርጅቱ ዋና ዳይሬክተር መዓዛ አበራ (ኢ/ር) እና የዩኒቨርሲቲው የምርምር እና ቴክኖሎጂ ምክትል ፕሬዝዳንት አብርሃም ደበበ (ዶ/ር) ናቸው።
የጋራ መግባቢያ ስምምነቱ ተቋማቱ በሰው ሀብት አቅም ግንባታ እና ልማት፣ የቴክኖሎጂ ሽግግር፣ የልማት መስኮች እና በጥራት ማረጋገጫ ዘርፍ በትብብር መስራት የሚያስችላቸው ነው።
ስምምነቱ ድርጅቱ በጥራት ማረጋገጥ ዘርፍ የልዕቀን ማዕከል ለመሆን የያዘውን ለማሳካት የሚያስችላው ወሳኝ እርምጃ መሆኑ ተገልጿል።
መዓዛ አበራ (ኢ/ር) የጋራ ትብብርን የሚያጠናክሩ ስምምነቶች ስራን ውጤታማ እንደሚያደርጉ መግለጻቸውን ከድርጅቱ የተገኘ መረጃ ያመለክታል።
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026
ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...
Apr 3, 2026
ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...
Mar 31, 2026
ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...
Mar 26, 2026