የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የአካባቢው ማህበረሰብ የሥራ ባህል እንዲቀየርና በሀብቱ ተጠቃሚ እንዲሆን ድጋፍ እናደጋለን

Mar 11, 2025

IDOPRESS

አሶሳ፤ መጋቢት 01/2017(ኢዜአ):- የአካባቢው ማህበረሰብ የሥራ ባህል እንዲቀየርና በሀብቱ ተጠቃሚ እንዲሆን ድጋፍ የሚያደርጉ መሆናቸውን በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የዳቡስ ወንዝን በመጠቀም በመስኖ እያለማ ያለው ድርጅት ገለጸ።


በክልሉ ኡንዱሉ ወረዳ በእርሻና መስኖ ልማት የተሰማራው የሮኤል የተቀናጀ እርሻና መስኖ ልማት ድርጅት የዳቡስ ወንዝን በመጠቀም የመስኖ ስራ እያከናወነ መሆኑን ነው የገለጸው።


የድርጅቱ ምክትል ማናጀር አቶ ማንእንደራስ ይንገስ እንዳሉት፤ ድርጅቱ የልማት ስራውን የጀመረው ከአራት ወራት በፊት ሲሆን በአሁኑ ወቅት አስር ሄክታር ማሳ ላይ ቲማቲም፣ ሽንኩርት እና ሀባብ እያለማ ይገኛል።


እየለማ ካለው አምስት ሄክታር የቲማቲም ማሳ ላይ እስከ 7 ሺህ 500 ኩንታል ምርት እንደሚጠብቁ ገልጸው፤ በቀጣይ በፍራፍሬ ምርቶች ላይ በስፋት ለመስራት የማሳ ዝግጅት ላይ መሆናቸውን ጠቁመዋል።


በተለይም ቤኒሻንጉል የሚታወቅበት የማንጎ ምርት ትልቁ እቅዳቸው መሆኑን አንስተዋል።


የዳቡስ ወንዝ በአካባቢው ያለው ለም አፈር ለመስኖ ልማት ስራቸው አመቺ በመሆኑ በልማቱ ውጤታማ እንደሚሆኑ ተስፋ ሰንቀዋል።


ድርጅቱ በእንስሳት እና ንብ እርባታ ለመሰማራት ቅድመ ዝግጅት እያደረገ መሆኑን ጠቅሰው በሁለት ሳምንት ጊዜ ውስጥ 200 ፍየሎችን እንደሚያስገቡም ተናግረዋል።


የአካባቢው ማህበረሰብ የስራ ባህል እንዲቀየር እና ህብረተሰቡ ምርቱን በአቅራቢያው እንዲያኝ ማድረግ የድርጅቱ ዓላማ እንደሆነም አብራርተዋል።


ድርጅቱ 80 ለሚደርሱ ዜጎች ቋሚ እና ጊዜያዊ የስራ ዕድል የፈጠረ ሲሆን የክልሉ ከፍተኛ አመራሮችም የድርጅቱን የሥራ እንቅሰቃሴ እንደሚከታተሉት ምክትል ማናጀሩ አስታውቀዋል።


የስራ ዕድል ከተፈጠረላቸው ወጣቶች መካከል ወጣት ገብረእግዚአብሔር ገብረእየሱስ እንደተናገረው በድርጅቱ በሚያገኘው ገቢ እራሱን እያስተዳደረ ነው።


ከዓረብ አገር ስደት መልስ በአገር ቤት የጀመረው ሥራ በመሆኑም ጥሩ አየር እየተነፈሰና እድገትን ሰንቆ በመስራት ላይ መሆኑን ተናግሯል።


ድርጅቱ በርካታ ባለሙያዎችን የያዘ መሆኑን የገለጸው ወጣቱ የተለያዩ ሙያዎችን እየተማሩ እንደሆነም ገልጿል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026