የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

ከተረጂነት በመላቀቅ የተሟላ ሀገራዊ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎች የታሪክ እጥፋት የሚያመጡ ናቸው - አቶ አደም ፋራህ

Mar 10, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 29/2017(ኢዜአ)፡- ከተረጂነት በመላቀቅ የተሟላ ሀገራዊ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎች የታሪክ እጥፋት የሚያመጡ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንትና የዋና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አደም ፋራህ ገለጹ።

ብልጽግና ፓርቲ ለሶስት ቀናት ሲያካሂድ የቆየውን የስድስት ወራት የስራ አፈጻጸም ግምገማ አጠናቋል።


ጉባኤው በሶስተኛ ቀን ውሎው ከተረጂነት አስተሳሰብ ለማላቀቅና የቤተሰብ ምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ተግባራዊ የሆነውን መርሃ ግብር አስመልክቶ በቀረበ የሱፐርቪዥን ስራዎች ሪፖርት ላይ ተወያይቷል።

የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንትና የዋና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አደም ፋራህ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ ከተረጂነት ለመላቀቅ የተጀመረው ምርታማነትን የማሳደግ ተግባር ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል።

በሀገር ደረጃ ተግባራዊ የተደረጉ እንደ ሌማት ትሩፋት፣ የከተማ ግብርና እና ሌሎች ኢኒሼቲቮች ማሳኪያ ግብ ሊሆኑ እንደሚገባም ጠቁመዋል።

ከተረጂነት የመላቀቅ ሀገራዊ ንቅናቄ ስራው ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ አመራሩ ለስራው የሰጠው ልዩ ትኩረት የሚበረታታ መሆኑን ነው የገለጹት።

ከተረጂነት መላቀቅ የአርበኝነት ምዕራፍ መሆኑን ያነሱት የፓርቲው ምክትል ፕሬዝዳንት፤ የቀጣይ ስራዎችን በፍጥነትና በመፍጠር መተግበር እንደሚገባ ተናግረዋል።

ከተረጂነት በመላቀቅ የተሟላ ሀገራዊ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ስራዎች የታሪክ እጥፋት የሚያመጡ መሆናቸውንም አመላክተዋል።


በብልጽግና ፓርቲ ዋና ጽህፈት ቤት የፖለቲካና አቅም ግንባታ ዘርፍ የፖለቲካ ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ ብሩክ ግዛው የሱፐርቪዥን ሪፖርቱን ባቀረቡበት ወቅት ከተረጂነት ለመላቀቅ እየተከናወኑ የሚገኙ ስራዎች ውጤት እያስገኙ መሆናቸውን ገልጸዋል።

መርሃ ግብሩን ማሳካት የሚያስችል ዕቅድ መዘጋጀቱን፣ የመግባባት ስራ በሁሉም ደረጃ መሠራቱን እንዲሁም ተጠቃሚዎች ከተረጂነት ለመውጣት ትክክለኛ አስተሳሰብ እንዲኖራቸው ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል።

በተለይም ሊያጋጥሙ የሚችሉ አደጋዎችን በራስ አቅም ምላሽ ለመስጠት በየደረጃው እየተደረጉ ያሉ ጥረቶች አበረታች መሆናቸውን ጠቁመዋል።

በሴፍቲኔት መርሃ ግብር ተጠቃሚ የሆኑ ዜጎች ዕድሉን በአግባቡ ተጠቅመው ከተረጂነት እንዲላቀቁ እየተደረገ ያለው ርብርብ አበረታች መሆኑን ገልጸዋል።

የንቅናቄ ስራው በሁሉም አካባቢዎች ያለው የግንዛቤ፣ የአመለካከትና የዝግጁነት ወጥነትን ማስተካከል እንደሚገባም ተናግረዋል።


የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር)፤ ከተረጂነት ወደ ምርታማነት የመሸጋገር ሂደት ከሃሳብ ወደ ተግባር መሸጋገር መጀመሩን ተናግረዋል።

ተረጂነትን ከመቅረፍ አኳያ ሰፊ ስራ መሰራቱን ጠቁመው፤ ክልሎች የመጠባበቂያ እህል ክምችትን ለማሳደግ መሠራት እንዳለባቸው ገልጸዋል።

አመራር አባላት ግብዓቶችን ለአርሶ አደሮች ተደራሽ ከማድረግ አኳያ ሰፊ ስራ መሥራት እንደሚጠበቅባቸው ጠቁመዋል።


የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽነር አምባሳደር ሽፈራው ተክለማርያም(ዶ/ር) በበኩላቸው ሰብዓዊ ድጋፍን በራስ አቅም ለመሸፈን የተጀመሩ ስራዎችን አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል ብለዋል።

የመጠባበቂያ እህል ክምችትን ማሳደግ ከሁሉም በላይ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት ተግባራዊ መደረግ እንዳለበትም ጠቁመዋል።


የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትር ጫልቱ ሳኒ በበኩላቸው፤ በከተማ ሴፍቲኔት የታቀፉ ዜጎች ሰርተው ራሳቸውን እንዲችሉ የቁጠባ ባህላቸው እንዲያድግ ሥራዎች እየተከናወኑ ናቸው ብለዋል።

በዚህም በተጨባጭ ለውጥ በማምጣት ለሌሎች አርዓያ መሆን የሚችሉ ዜጎች ማውጣት መጀመሩን ጠቁመዋል።

በውይይቱ ተሳታፊዎች በሁሉም ክልሎች ከተረጂነት ለመላቀቅ የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ጠቁመው፤ የታለመውን ዓላማን ከግብ ለማደረስም ተጨማሪ ርብርብ እንደሚደርግም አብራርተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...

Feb 28, 2025

<p>በዞኑ በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ ነው</p>

ደሴ፤ የካቲት 16/2017 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት የተሻለ ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓሊ መኮንን ገለ...

Feb 24, 2025

<p>የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተደረገ ነው - ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል</p>

አሶሳ ፤ የካቲት 15/2017(ኢዜአ):- የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ችግር ፈቺ ስራዎችን እንዲያከናውኑ እየተሰራ መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ገ...

Feb 24, 2025

<p>ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች ነው -የገንዘብ ሚኒስትር አህመድ ሽዴ</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 4/2017(ኢዜአ)፡- ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ቀንድ የልማት ትስስርና የኢኮኖሚ ውህደት የመሪነት ሚናዋን እየተወጣች እንደምትገኝ የአፍሪካ ቀንድ...

Feb 12, 2025