
አዳማ ፤ የካቲት 20/2017( ኢዜአ)፦ አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የልህቀት ማዕከላቱን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ለማደራጀት የሚያስችለውን ስምምነት ከደቡብ ኮሪያው ሳምሳንግ ኩባንያ ጋር ዛሬ ተፈራረመ።
የልህቀት ማዕከላቱ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ መደራጀት የሀገሪቷን የኢንዱስትሪ ልማት በዘመናዊ የምርምር ቴክኖሎጂ ውጤቶችና ግኝቶች ለመደገፍ እንደሚያስችለው ተገልጿል።

የተሽከርካሪ መገጣጠሚያ፣ ፋርማሲዩቲካል፣ ኤሌክትሮኒክስ፣ አድቫንስ ማኑፋክቸሪንግና አድቫንስ ማቴሪያል ደግሞ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ እንዲደራጁ አምስቱ የዩኒቨርሲቲው የልህቀት ማዕከላት መሆናቸው ታውቋል።
ለእነዚህ የልህቀት ማዕከላት ዘመኑ የደረሰበትን ዘመናዊ ቴክኖሎጂ ለማሟላት የሚያስችለው ስምምነት ነው ከደቡብ ኮሪያው የሰምሳንግ ቴክኖሎጂ ኩባንያና ኮንሰርቲየም ጋር ዛሬ የተፈራረሙት።
የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ለሚ ጉታ (ዶ/ር) በወቅቱ እንደገለፁት የልህቀት ማዕከላቱን የምርምር ፓርክ አሁን የዓለም የምርምር ቴክኖሎጂ ደረጃ በደረሰበት የላቦራቶሪ መሳሪያዎች ለማደራጀት የዛሬው ስምምነት ተፈርሟል።
''የላቦራቶሪ ግብዓቱ ግዥ በረዥም ጊዜ ብድር ከደቡብ ኮሪያ በተገኘው 100 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ከሰምሳንግ ኩባንያ ጋር ተፈራርመናል'' ብለዋል።
በኩባንያው በኩል የምርምር ላቦራቶሪ መሳሪያዎችን የመገጣጠም ስራ በአንድ ዓመት ውስጥ እንደሚጠናቀቅ ገልጸዋል።
የሳምሰንግ ኮንስትራክሽንና ትሬዲንግ ኮርፖሬሽን የምስራቅ አፍሪካ ስራ አስኪያጅ ቹልሱን ሀዋንግ በበኩላቸው ኩባንያው የላብራቶሪ ቴክኖሎጂዎችና የምርምር መሳሪያዎችን በቅርቡ የማደራጀት ስራ ይጀመራል ብለዋል።
የልህቀት ማዕከላቱ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን በሁለት ዓመት ጊዜ ውስጥ የማደራጀት ስራውን እንደሚያጠናቀቅም ገልጸዋል።
ኩባንያው ከመሳሪያዎች መገጣጣም ባሻገር የመብራት፣ ውሃ፣ የውስጥ መስመሮች እና የላቦራቶሪ ማስተዳደር የሚያግዙ ሶፍትዌሮች እንደሚያለማ ተገልጿል።
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026
ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...
Apr 3, 2026
ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...
Mar 31, 2026
ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...
Mar 26, 2026