የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

<p>ዩኒቨርሲቲው የልህቀት ማዕከላቱን በቴክኖሎጂ ለማዘመን የሚያስችል ስምምነት ተፈራረመ</p>

Feb 28, 2025

IDOPRESS

አዳማ ፤ የካቲት 20/2017( ኢዜአ)፦ አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የልህቀት ማዕከላቱን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ ለማደራጀት የሚያስችለውን ስምምነት ከደቡብ ኮሪያው ሳምሳንግ ኩባንያ ጋር ዛሬ ተፈራረመ።

የልህቀት ማዕከላቱ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ መደራጀት የሀገሪቷን የኢንዱስትሪ ልማት በዘመናዊ የምርምር ቴክኖሎጂ ውጤቶችና ግኝቶች ለመደገፍ እንደሚያስችለው ተገልጿል።


የተሽከርካሪ መገጣጠሚያ፣ ፋርማሲዩቲካል፣ ኤሌክትሮኒክስ፣ አድቫንስ ማኑፋክቸሪንግና አድቫንስ ማቴሪያል ደግሞ በዘመናዊ ቴክኖሎጂ እንዲደራጁ አምስቱ የዩኒቨርሲቲው የልህቀት ማዕከላት መሆናቸው ታውቋል።

ለእነዚህ የልህቀት ማዕከላት ዘመኑ የደረሰበትን ዘመናዊ ቴክኖሎጂ ለማሟላት የሚያስችለው ስምምነት ነው ከደቡብ ኮሪያው የሰምሳንግ ቴክኖሎጂ ኩባንያና ኮንሰርቲየም ጋር ዛሬ የተፈራረሙት።

የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ለሚ ጉታ (ዶ/ር) በወቅቱ እንደገለፁት የልህቀት ማዕከላቱን የምርምር ፓርክ አሁን የዓለም የምርምር ቴክኖሎጂ ደረጃ በደረሰበት የላቦራቶሪ መሳሪያዎች ለማደራጀት የዛሬው ስምምነት ተፈርሟል።

''የላቦራቶሪ ግብዓቱ ግዥ በረዥም ጊዜ ብድር ከደቡብ ኮሪያ በተገኘው 100 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ከሰምሳንግ ኩባንያ ጋር ተፈራርመናል'' ብለዋል።

በኩባንያው በኩል የምርምር ላቦራቶሪ መሳሪያዎችን የመገጣጠም ስራ በአንድ ዓመት ውስጥ እንደሚጠናቀቅ ገልጸዋል።

የሳምሰንግ ኮንስትራክሽንና ትሬዲንግ ኮርፖሬሽን የምስራቅ አፍሪካ ስራ አስኪያጅ ቹልሱን ሀዋንግ በበኩላቸው ኩባንያው የላብራቶሪ ቴክኖሎጂዎችና የምርምር መሳሪያዎችን በቅርቡ የማደራጀት ስራ ይጀመራል ብለዋል።

የልህቀት ማዕከላቱ የምርምር ቴክኖሎጂዎችን በሁለት ዓመት ጊዜ ውስጥ የማደራጀት ስራውን እንደሚያጠናቀቅም ገልጸዋል።

ኩባንያው ከመሳሪያዎች መገጣጣም ባሻገር የመብራት፣ ውሃ፣ የውስጥ መስመሮች እና የላቦራቶሪ ማስተዳደር የሚያግዙ ሶፍትዌሮች እንደሚያለማ ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026