የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

<p>የክልሉ መስኖ ልማት ገበያ በማረጋጋትና በስራ ዕድል ፈጠራ ጉልህ ሚና እየተጫወተ ነው- የምክር ቤት አባላት</p>

Feb 26, 2025

IDOPRESS

ሀዋሳ፤ የካቲት 18/2017(ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል እየተከናወነ ያለው የመስኖ ልማት ገበያ በማረጋጋትና በስራ ዕድል ፈጠራ ጉልህ ሚና እየተጫወተ በመሆኑ ተጠናክሮ እንዲቀጥል የክልሉ ምክር ቤት አባላት አሳሰቡ፡፡

የሲዳማ ክልል ምክር ቤት አባላት በሰሜናዊ ሲዳማ ዞን እና በሃዋሳ ከተማ የተከናወኑ የመስኖ እና ሌሎች የልማት ስራዎችን ተመልክተዋል፡፡

በምልከታቸውም የመስኖ ልማት ስራዎች ገበያን ማረጋጋት እና ሰፊ የስራ ዕድል በመፍጠር ያላቸውን ጉልህ ሚና ገልጸዋል።

ከምክር ቤት አባላት መካከል አቶ ሚሊዮን ዮሳ እና ወይዘሮ ኤልሳቤት ፍቼ ለኢዜአ እንዳሉት በግብርናው መስክ የልማት ስራዎች የህዝቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጡ ናቸው።

ለአብነትም መስኖ ልማቱ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ፣ ኢኮኖሚን ለማሳደግና የስራ ዕድል ለመፍጠር ያለውን ጉልህ ሚና አንስተዋል።

ጦም ያደረ ሰፊ መሬትን በመስኖ ማልማት ምርታማነትን መጨመር መቻሉን ጠቅሰው፤ በሁሉም የክልሉ አካባቢዎች በማስፋት የህዝቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡

አቶ ታረቀኝ ታምሬ በበኩላቸው የግብርና ልማቱ የአርሶ አደሩን ኢኮኖሚ አቅም የሚያሳድግና የህዝቡን ኑሮ የሚያረጋጋ እንደሆነ ጠቁመዋል።

የተጀመሩ የመስኖ ልማት ስራዎች በቀጣይነት እንዲስፋፉ ምክር ቤቱ ክትትሉን እንደሚያጠናክር አረጋግጠዋል።

የክልሉ ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባኤ አቶ ዘነበ ዘርፉ፤ የምክር ቤት አባላቱ በሁለት ቡድን በሰሜናዊ ሲዳማ ዞን የተለያዩ ወረዳዎችና በሃዋሳ ከተማ የመስክ ምልከታ ማድረጋቸውን ገልጸዋል፡፡

የምክር ቤት አባላቱ ከሪፖርት ባለፈ በተጨባጭ የተሰሩ ስራዎችን በመስክ ምልከታ ለማረጋገጥ ያስችላቸዋል ብለዋል፡፡

የተጀመሩ የልማት ስራዎች በሁሉም አካባቢዎች እንዲስፋፉና ቀጣይነት እንዲኖራቸው ምክር ቤቱ በትኩረት ይሰራል ነው ያሉት።

የሲዳማ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 8ኛ መደበኛ ጉባዔውን ነገ ይጀምራል።፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026