
ደምቢ ዶሎ፤ የካቲት 14/2017(ኢዜአ)፦ የደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ የአካባቢው ነዋሪዎች በሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር ተጠቃሚ እንዲሆን እገዛ እያደረገ መሆኑን አስታወቀ፡፡
የዩኒቨርሲቲው አስተዳዳር እና ቢዝነስ ልማት ምክትል ፕሬዚዳንት ገመቺስ ብርሃኑ (ዶ/ር) ለኢዜአ አንደተናገሩት ዩኒቨርሲቲው የተማረ የሰው ሀብት ከማፍራት በተጓዳኝ የምርምርና የማህበረሰብ አገልግሎት በትኩረት እያከናወነ ይገኛል፡፡
በተለይም የአካባቢውን ነዋሪ ተጠቃሚ ለማድረግ በትምህርት፣ በግብርናና በማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ሰፋፊ ስራዎች እየሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በተለይም የአካባቢው ነዋሪዎች በእንሰሳት፣ በዓሳ እና በአሳማ እርባታ ተጠቃሚ እንዲሆኑ በምርምር የተገኙ የተሻሻሉ ዝርያዎች እያቀረበ መሆኑን ገልጸዋል።
በቡና፣ በአትክልት እና ፍራፍሬ እና በሌሎችም የግብርና ዘርፎች በዩኒቨርሲቲው የምርምር ማዕከሎች የተገኙ የተሻሻሉ ዝርያዎች እየቀረቡ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ዩኒቨርሲቲው በ10 ሄክታር መሬት ላይ የተለያዩ የግብርና ስራዎች እያከናወነ መሆኑን አንስተው የአካባቢውን ማህበረሰብ ከማገዝ ባሻገር ዩኒቨርሲቲው በራሱ አቅም ገቢ ለማመንጫት ጥረት እያደረገ መሆኑንም አክለዋል።

በተጨማሪም በቄለም ወለጋ ዞን በኢኒሼቲቭ መልክ የሚተገበረውን የንብ ማነብ ስራ ለማገዝ የተለያዩ ድጋፎች እተቀረበ መሆኑን ጨምረው ገልጸዋል።
የደምቦ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ ግብርና ምርምር ማዕከል ዳይሬክተር ሶሬሳ ሹማ፣ ዩኒቨርስቲው የሚደግፈው የአሳ እርባታ ስራ የአካባቢው ነዋሪ ተጨማሪ ገቢ እንዲያገኝ እያስቻለ ነው ብለዋል።

ከእንስሳት እርባታ ባሻገር ነዋሪው የአሳ እርባታ ስራን እንዲለማመድ በተደረገው እገዛ ማህበረሰቡ የተመጣጠነ የምግብ እንዲያገኝ እድል መፈጠሩንም ተናግረዋል።
ዩኒቨርስቲው የሚያከናውናቸው የግብርና ምርምር ስራዎች በአካባቢው የሌማት ትሩፋትን ከማገዝ ጎን ለጎን ለወጣቶች የስራ እድል መፈጠሩንም ገልጸዋል።
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026
ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...
Apr 3, 2026
ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...
Mar 31, 2026
ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...
Mar 26, 2026