የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

<p>የክልሉን ሃብትና ጸጋ በመለየት ለዜጎች   የሥራ እድል መፍጠር  የሁልጊዜ ተግባራችን ነው - አህመዲን መሐመድ(ዶ/ር)</p>

Feb 20, 2025

IDOPRESS

ደሴ ፤ የካቲት 12/2017(ኢዜአ)፡ -የአማራ ክልልን ሃብትና ጸጋ በመለየት ለዜጎች የሥራ እድል መፍጠር የሁልጊዜ ተግባራችን ነው ሲሉ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የክልሉ ከተሞች ልማት ክላስተር አስተባባሪና የከተማና መሰረት ልማት ቢሮ ኃላፊ አህመዲን መሐመድ (ዶ/ር)ገለጹ።

የክልሉ ሥራና ስልጠና ቢሮ የ2017 በጀት ዓመት የስድስት ወራት ሥራ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ በኮምቦልቻ ከተማ እየተካሄደ ነው።


በመድረኩ ላይ የተገኙት አህመዲን መሐመድ(ዶ/ር) እንደተናገሩት፤ በክልሉ ቴክኖሎጂን መሰረት ያደረገ የሥራ እድል ፈጠራና የእውቀት ሽግግርን ለማረጋገጥ እየተሰራ ነው።

በዚህም በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች ያለውን ሃብትና ጸጋ በመለየት ለዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ እድል መፍጠር የሁልጊዜ ተግባራችን ነው ብለዋል።

ሰላምና የሥራ እድል የማይነጣጠሉ የክልሉ የትኩረት አጀንዳዎች መሆናቸውን ጠቅሰው፤ በግማሽ በጀት ዓመቱ በዚህ ተግባር ላይ በመረባረብ አበረታች ውጤት መስመዝገብ መቻሉን ገልጸዋል።

በኮደርስ ስልጠና፣ በኮሪደርና ኢንዱስትሪ ልማት ላይ ወጣቱን በማሰማራት በቴክኖሎጂ የበቃና ተወዳዳሪ የሰው ሀይል ለመገንባት ባለድርሻ አካላት በቅንጅት መስራት ይኖርብናል ብለዋል።


የአማራ ክልል ሥራና ስልጠና ቢሮ ኃላፊ ስቡህ ገበያው(ዶ/ር) በበኩላቸው ፤ በክልሉ የሥራ እድል መፍጠሪያ ፀጋዎችን በመለየት ዜጎችን ተጠቃሚ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

በዚህም በቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጅች በአጭር፣ በመካከለኛና በረጅም ጊዜ ስልጠና በመስጠት በበጀት ዓመቱ ከታቀደው ውስጥ ባለፉት ሰባት ወራት ከ500 ሺህ ለሚበልጡ ሰዎች በተለያዩ የስራ መስኮች የሥራ እድል መፍጠር መቻሉን ገልጸዋል

የብድር፣ የመስሪያና የመሸጫ ቦታ፣ የገበያ ትስስር በመፍጠር ኢንተርፕራይዞችን ወደ ባለሃብትነት እንዲሸጋገሩና ተጨማሪ የሥራ እድል እንዲፈጥሩ ድጋፍ እየተደረገ ነው ብለዋል።


በከተማው ለዜጎች የሥራ እድል በመፍጠር ኢኮኖሚውን ለማነቃቃት ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ይገኛል ያሉት የኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ መሀመድአሚን የሱፍ ናቸው።

ዛሬን ጨምሮ ለሁለት ቀናት በሚቆየው መድረክ የክልል፣ የዞን፣ የከተማና የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጆች አመራር አባላትና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ ነው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026