የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

<p>ኢትዮጵያና ሩሲያ ያላቸውን ስትራቴጂካዊ አጋርነት ይበልጥ ለማሳደግ ቁርጠኛ መሆናቸውን ገለፁ</p>

Feb 20, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 12/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያና ሩሲያ ጋር ያላቸውን ስትራቴጂካዊ አጋርነት ይበልጥ ለማሳደግ ቁርጠኛ መሆናቸውን ገለፁ።

በኢትዮጵያ መንግስት እና በሩሲያ መንግስት የመጀመሪያው የኒውክለር ቴክኖሎጂ ፍኖተ ካርታ ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ መደረጉን ተከትሎ ለመጪዎቹ 3 ዓመታት የሚያገለግል ሁለተኛው ፍኖተ ካርታ በዛሬው ዕለት ተፈርሟል።

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ኢትዮጵያ እና ሩስያ በኢኮኖሚያዊ ትብብር፣ በባህል ልውውጥ፣ በቴክኖሎጂ ፈጠራዎችና ሽግግር፣ በኢንቨስትመንት፣ በትምህርት፣ በግብርና በንግድ ልውውጥ እና በመሰረተ ልማት ዝርጋታ ዘርፎች ላይ ይበልጥ ግንኙነታቸውን ለማጠናከር ያለመ የምክክር መድረክ አካሂደዋል።

የምክክር መድረኩ ዓላማ የኢትዮጵያና የሩስያ የሁለትዮሽ ግንኙነትን ከመቼውም በላይ ከፍ በማድረግ የጋራ ስምምነቶችን ለመፍጠር ያለመ ነው።

ከኢትዮጵያ በኩል የኢትዮ-ሩሲያ የበይነ መንግስታቱ የጋራ ኮሚቴ ጣምራ ሰብሳቢ የሆኑት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ(ዶ/ር) ኢትዮጵያ ከሩሲያ ፌዴሬሽን ጋር የምትጋራውን ለዘመናት ያስቆጠረ እና ታሪካዊ ግንኙነትን ከፍ ለማድረግ እየተደረገ ያለው ጥረት እጅግ ፍሬማ ነው ብለዋል።

ከዚህ በፊት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በሩሲያ ያደረጉት ጉብኝት የሀገራቱን ግንኙነትን በማጠናከር የጋራ መግባባትና አጋርነት ማሳደጉን ገልፀዋል።

በኢትዮጵያ እና በሩሲያ መካከል ያለው ወዳጅነት የዘመናት ግንኙነት ውጤት ነው ያሉት ሚኒስትሩ፤ የምናከናውናቸው የአጋር ስምምነቶች የዛሬውን አንገብጋቢ ጉዳዮች ከማንሳት ባለፈ ለቀጣይ ትውልዶች ጸንቶ የሚዘልቅና የሚለመልም አጋርነት መሰረት የሚጥል መሆኑን አስገንዝበዋል።

ከሩሲያ በኩል የበይነ_መንግስታት የጋራ ኮሚቴው ጣምራ ሰብሳቢ የሆኑት የኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትሩ ማክሲም ሬሽቴንኮቭ በበኩላቸው ሩሲያ ከኢትዮጵያ ጋር በአጋርነት ሰፊ ሰራዎች እየሰራች መሆኑን ጠቁመዋል።

በቀጣይም ግንኙነቱን ይበልጥ በማጠናከርና በመቀራረብ ዘርፈ ብዙ ስራዎች ለመስራት ከፍተኛ ፍላጎት እንዳላቸውም መግለፃቸውን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።

በመሆኑም በንግድ፣ በጤና፣ በባንክ ስርዓት፣ በኢነርጂ፣ በቴክኖሎጂ፣ በማስ ሚዲያ፣ በቱሪዝምና ንግድ በሌሎችም ዘርፎች ለመስራት በጋራ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ እንደሚተጉ አረጋግጠዋል።

በምክክሩ ላይ የጤና፣ የቱሪዝም፣ የንግድና ቀጠናዊ ትስስር፣ የትምህርት፣ የውጪ ጉዳይ፣ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች እና የሌሎች ተቋማት ከፍተኛ አመራሮች ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026