
አዲስ አበባ፤ የካቲት 11/2017(ኢዜአ)፦ በፀጥታና ደህንነት በኢኮኖሚና በፖለቲካው መስክ የተከናወኑ ተግባራት ሀገር አሻጋሪ መሆናቸውን ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ።
የጠቅላይ ሚኒስትር ተጠሪ ተቋማት የ2017 በጀት ዓመት የመጀመሪያው አጋማሽ አፈጻጸም የግምገማ መድረክ እየተካሄደ ነው።
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በመክፈቻ ንግግራቸው፥ በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያው አጋማሽ በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚና ሌሎችም መስኮች በርካታ ስኬቶች መመዝገባቸውን ገልጸዋል።
በብልፅግና ፓርቲ የሚመራው የለውጡ መንግሥት ከተመሠረተ በአጭር ጊዜ ውስጥ የላቁ ተግባራትን ማከናወኑንም ጠቅሰዋል።

በተለይም በፀጥታና ደህንነት በኢኮኖሚና በፖለቲካው መስክ የተከናወኑ ተግባራት ሀገር አሻጋሪ ናቸው ብለዋል።
ብዙ ፈተናዎች ቢገጥሙንም እየተሻገርናቸው ነው ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ፥ በቀጣይም ፈተናዎችን ለተሻገረ ድል መትጋት ወሳኝ ነው ብለዋል።
በግማሽ ዓመቱ ከልማት ሥራዎች ባሻገር በርካታ ሀገራዊ፣ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ሁነቶችንና ጉባኤዎችን ማስተናገድ መቻሉንም ተናግረዋል።
የኢትዮጵያን ገፅታ የቀየሩና ስሟን በበጎ ያስጠሩ ስራዎች መከናወናቸውን በማንሳት፥ በዓመቱ በዓለም ከፍተኛ የቱሪስት መዳረሻ ከሆኑ ሀገራት አንዷ ሆናለች ብለዋል።
በድህነትና ኋላቀርነት ትታወቅ የነበረችው ሀገራችን ዓይን ገላጭ ሥራዎችን በመተግበር በበርካታ መስኮች አስደማሚ ለውጥ አምጥታለች ብለዋል።

ለተገኙ ተስፋ ሰጪ ስኬቶች የጠቅላይ ሚኒስትር ተጠሪ ተቋማት የመሪነት ድርሻቸው የላቀ እንደሆነም ገልጸዋል።
የእስካሁን ሥራዎች ጅምር እንጂ የተሟላ የስኬት ደረጃ ላይ አልደረሱም ያሉት አቶ ተመስገን፥ የዓለም ነባራዊ ሁኔታን ታሳቢ ያደረገ ሥራ ከፊታችን ይጠብቀናል ብለዋል።
ኢትዮጵያ በሁሉም መስክ ራሷን እንድትችል እና በአፍሪካ የብልፅግና ተምሳሌት እንድትሆን የተቀናጀና እረፍት የለሽ ሥራ የግድ መሆኑን ጠቅሰዋል።
የጠቅላይ ሚኒስትር ተጠሪ ተቋማት ከራሳቸው ባለፈ ለሌሎች ተቋማት ግብ መሳካት ጉልህ አስተዋፅኦ ማበርከት እንዳለባቸውም ገልፀዋል።
በተለይ አገልግሎት አሰጣጥን ማዘመን፣ ወጪ ቆጣቢ መሆን፣ ቅንጅታዊ አሠራርን ማጠናከር እና ተፅዕኖ መፍጠር ላይ ተጠሪ ተቋማቱ የትኩረት ማዕከል መሆን አለባቸው ብለዋል።
አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...
Apr 9, 2026
ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...
Apr 3, 2026
ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...
Mar 31, 2026
ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...
Mar 26, 2026