የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

<p>የቦንጋ፣ ሚዛን አማን እና ታርጫ ከተሞች የኮሪደር ልማት ሥራ የከተሞቹን ገጽታ በመቀየር ለኢንቨስትመንት ተመራጭ አድርጓቸዋል</p>

Feb 19, 2025

IDOPRESS

ሚዛን አማን፣ ታርጫ፣ ቦንጋ የካቲት 11/2017 (ኢዜአ )፡-በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ቦንጋ፣ ሚዛን አማንና ታርጫ ከተሞች እየተከናወኑ ያሉ የኮሪደር ልማት ሥራዎች የከተሞቹን ገጽታ በመቀየር ለኢንቨስትመንት ተመራጭ እያደረጋቸው መሆኑን የከተማዎቹ ከንቲባዎች ተናገሩ።

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው የኮሪደር ልማት ሥራ ከተሞችን ውብ፣ ፅዱና ለነዋሪዎች ምቹ ከማድረግ ባለፈ ለኢንቨስትመንትም ተመራጭ እንዲሆኑ እያስቻለ ነው።

ኢዜአ ያነጋገራቸው በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የሚዛን አማን፣ የቦንጋ እና የታርጫ ከተማ አስተዳደር ከንቲባዎች እንዳሉት፣ ቀደም ሲል ከተሞቹ በፕላን ባለመመራታቸው የህብረተሰቡን የአገልግሎት ጥያቄ ለመመለስ እንቅፋት ሆኖባቸው ቆይቷል።

በሚዛን አማን ከተማ እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት የህብረተሰቡን የሥራ ባህልና የከተማዋን ገጽታ እየቀየረ መምጣቱን የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ አቶ ግሩም ተማም ተናግረዋል።


በተጨማሪም የከተማዋ የቱሪዝም እንቅስቃሴ እንዲጨምር፣ ለኢንቨስትመንት ተመራጭ እንድትሆንና ለነዋሪዎች ምቹ እንድትሆን እያደረጋት መሆኑን ገልጸዋል።

በከተማው ፕላን መሰረት የኮሪደር ልማት ሥራው እንደሚከናወን ለህብረተሰቡ ቀድሞ ግንዛቤ በመፈጠሩ በአሁኑ ወቅት የሥራ አፈጻጸሙ አበረታች መሆኑን ገልጸዋል።

የቦንጋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ አስማማው አደመ በበኩላቸው፣ የቦንጋ ከተማ ከተመሰረተች በርካታ ዓመታት ብታስቆጥርም የዕድሜዋን ያክል ባለመልሟቷ ውበቷ ተደብቆ መቆየቱን አንስተዋል።


በአሁኑ ወቅት በከተማ አስተዳደሩ፣ በነዋሪውና በአጋር አካላት ተሳትፎ እየተከናወነ ያለው የኮሪደር ልማት ሥራ ከተማዋን ውብና ለኑሮ ምቹ እያደረጋት መሆኑ ጠቅሰዋል።

በዚህም በመጀመሪያው ዙር በ21 ሚሊዮን ብር የኮሪደር ልማት ሥራ መከናወኑን ጠቁመዋል።

የኮሪደር ልማቱ የመዝናኛ ፓርክ፣ የእግረኛ መንገድና እና ሌሎች አገልግሎቶችን ያካተተ መሆኑንም አብራርተዋል።


ከተማዋን የማስዋብ ሥራ መጀመሩን የገለጹት የታርጫ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ዳዊት ወንድሙ በበኩላቸው፣ የኮሪደር ልማቱ የመንገድ አካፋዮች፣ የመንገድ ዳር መብራት ዝርጋታና የህዝብ መዝናኛ ስፍራዎችን አካቶ እየተከናወነ መሆኑን ጠቁመዋል።


በተጨማሪ የእግረኛ መንገድና ሌሎች ልማቶች አካትቶ በተቀናጀ መንገድ የሚሰራው የኮሪደር ልማት ዘመን ተሻጋሪና መጪው ትውልድን ታሳቢ ያደረገ መሆኑንም ከንቲባው አክለዋል።

የከተሞቹ ከንቲባዎች ለኮሪደር ልማት ሥራው ስኬታማነት ህብረተሰቡ ንብረቱን በማንሳት ቦታውን ነጻ ከማድረግ ጀምሮ የተለያዩ እገዛዎችን እያደረገ መሆኑን ገልጸዋል።


ይህ ድጋፍ በቀጣይም ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጥሪ አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026