የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

<p>በግብርናው ዘርፍ የኢትዮጵያና ዩናይትድ ኪንግደምን የንግድ ትብብር የሚያጠናክር ስምምነት ተፈረመ</p>

Feb 18, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 10/2017(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ እና የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን ከዩናይትድ ኪንግደም አሴት ግሪን ኩባንያ ጋር የተቀናጀ የወተት ልማትና የንግድ እርሻ ፕሮጀክትን ለመጀመር የሚያስችል የ600 ሚሊዮን ዶላር ስምምነት ተፈራረሙ።

በፊርማ ስነ ስርዓቱ ላይ የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ እና የእንግሊዝ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አንጄላ ሬይነር ተገኝተዋል።

በስምምነቱ መሠረት አሴት ግሪን 51 በመቶ ድርሻ እንዲሁም የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ እና የኢትዮጵያ ግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን ደግሞ 49 በመቶ ድርሻ መያዛቸው ተነግሯል።

የግብርና ሚኒስትሩ ግርማ አመንቴ(ዶ/ር)፤ በዚህ ወቅት ፕሮጀክቱ ግብርናውን ለማዘመንና የቴክኖሎጂ እውቀትን ለአርሶ አደሮች ለማስተላለፍ ጉልህ ፋይዳ እንደሚኖረው ለስኬታማነቱም የበኩላችንን እንወጣለን ብለዋል።

የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ብሩክ ታዬ(ዶ/ር) በበኩላቸው እንደተናገሩት፤ ስምምነቱን በውጤታማነት ለመተግበር እንሰራለን ነው ያሉት ።

የአሴት ግሪን ቺፍ ኢንቨስትመንት ኦፊሰር፣ አልበርት ፍሪሸንላገር፤ ስምምነቱ በአፍሪካ ግዙፍ የወተት ልማት ፕሮጀክትን መተግበር የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል።

በኢትዮጵያ ጥራት ያለው የወተት ምርታማነትን በማሳደግና የግብርና ዘርፉን በቴክኖሎጂ በማዘመን የሚጨበጥ ውጤት ለማምጣት እንደሚሠሩ ገልጸዋል።

የስምምነቱ ዓላማ ምርታማነትን፣ ውጤታማነትንና ዘላቂነትን የሚያሳድጉ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የተሻለ የግብርና ስርዓት መገንባት መሆኑን ገልጸዋል።

ይህ ግዙፍ ስትራቴጂክ ስምምነት በሁለት ምዕራፎች እንደሚተገበር ተገልጿል።

በመጀመሪያው ምዕራፍ ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የወተት ልማት ማቀነባበሪያ ከመኖ ልማት ጋር ያካተተ ሲሆን ለዚህም 10 ሺህ የወተት ላሞችን የሚይዝ ማዕከልን ለመገንባት ታቅዷል።

በሁለተኛው ምዕራፍ የጋራ ኢንቨስትመንቱን በማስፋት የማቀነባበሪያ መሰረተ ልማቶች ወደ ተሟሉለት የጥጥ፣ የቅባት እህሎች እና የሩዝ እርሻ ለማሳደግም ግብ ተይዟል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር ተሸፍኗል

አዶላ ፤መጋቢት 30/2018 (ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በበልግ አዝመራ ከ260 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በዘር መሸፈኑን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት ገለጸ...

Apr 9, 2026

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026