
ባህርዳር፤ የካቲት 3/2017(ኢዜአ)፡- የብልጽግና ፓርቲ በ2ኛው ጉባኤ ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት የተሳለጠና ዘመናዊ የሲቪል ሰርቪስ አገልግሎት ለመስጠት በትኩረት እንደሚሰራ የአማራ ክልል ሲቪል ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ኮሚሽን አስታወቀ።
ኮሚሽኑ በብልጽግና ፓርቲ የመጀመሪያ ጉባኤ በተቀመጠው አቅጣጫ መሰረት በተከናወኑ ተግባራትና በ2ኛው ጉባኤ አቅጣጫዎች ላይ ማምሻውን የኮሚሽኑ ኮሚሽነር ወይዘሮ ባንቻምላክ ገብረ ማሪያም መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫቸውም በመጀመሪያው ጉባኤ የሲቪል ሰርቪስ ተቋማት ነጻና ገለልተኛ በሆነ መንገድ አገልግሎት እንዲሰጡ አቅጣጫ ተቀምጦ እንደነበር አስታውሰዋል።
በዚህም የተቋማትን አገልግሎት አሰጣጥ ችግር፣ መንስኤና የመፍትሄ አቅጣጫ የሚያመላክት ጥናት እስከ ወረዳ ድረስ መከናወኑን ገልጸዋል።
የመጀመሪያው የፓርቲው ጉባኤ የትግበራ ጊዜ ሲቪል ሰርቪሱን ለማዘመን እንደ ዝግጅት ምዕራፍ መወሰዱን ጠቁመው በቀጣይ የጥናቱን ግኝት መሰረት በማድረግ ወደ ተግባር ይገባል ብለዋል።
ለዚህም የብልጽግና ፓርቲ በ2ኛው ጉባኤ ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት የተሳለጠና ዘመናዊ የሲቪል ሰርቪስ አገልግሎት ለመስጠት በቁርጠኝነት እንደሚሰራ አስታውቀዋል።
በተለይም በየተቋማቱ ያለውን ሰራተኛ የአቅም ክፍተት መሙላት የሚያስችል ስራ እንደሚከናወን ጠቁመው ከዚህ ጎን ለጎንም ተጠያቂነትን ለማስፈን ይሰራል ነው ያሉት።
በክልሉ ያለውን የሲቪል ሰርቪስ አገልግሎት ዘመናዊ፣ ቀልጣፋና ፍትሃዊ በማድረግ የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ማቃለል በሚያስችል መልኩ እንደሚፈጸምም በመግለጫቸው አመላክተዋል።
ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...
Apr 3, 2026
ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...
Mar 31, 2026
ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...
Mar 26, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025