የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

<p>የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን የትራንስፖርት ዘርፍ ተዋናዮችን የሚያገናኝ የዲጂታል መተግበሪያ አስጀመረ</p>

Feb 11, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ የካቲት 3/2017(ኢዜአ)፦በትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን የለማ የትራንስፖርት ኦፕሬተሮችንና የጭነት ባለቤቶችን የሚገናኝ የዲጂታል መተግበሪያ አስጀምሯል።

በማሪታይም ባለስልጣን ስትራቴጂና ፖሊሲዎች ውስጥ ከተጠቅሱ የመፍትሄ ሃሳቦች ውስጥ በትራንስፖርት ዘርፍ የሚስተዋሉ የድለላና የቅንጅት ጉድለቶችን መስመር በማስያዝ ተዋናዮችን የሚያገናኝ መተግበሪያ በማፍለቅ ጥቅም ላይ እንዲውል መደረጉ ተገልጿል።

በዚህም የትራንስፖርትና ሎጂስቲከስ ሚኒስቴር፣ የባለስልጣኑ፣ የግሉ ዘርፍ እንዲሁም በመንግስት-የግል አጋርነት የሚፈጸሙ 40 የሚደርሱ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ፕሮጀክቶችን ጥቅም ላይ ማዋሉ ተገልጿል።

ፕሮጀክቶቹ በዘርፉ የመሰረተ ልማት ግንባታን፣ የአገልግሎት ማቀላጠፈያ ሥርዓትን፣ የጭነት እና የህዝብ ትራንስፖርት የአገልግሎት አቅም ግንባታ መርሃ ግብሮች የሚሳለጡበት እንደሆኑ ተነስቷል።

በዚህም መተግበሪያው በመንግስት ክትትል የግሉን ዘርፍ በማሳተፍ ያለውን የመረጃ ግንኙነት እና አገልግሎት የማሳልጥ የቴክኖሎጂ የአሰራር ሥርዓት መሆኑ ተመላክቷል።

መተግበሪያው በዩናይትድ አፍሪካ ሎጂስቲክስ የቴከኖሎጂ ኩባንያ እና ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ በሰራው ስኬታማ ተግባር የተቀናጀ የቴክኖሎጂ ሥርዓት "Digital Freight Marketplace systems" የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል።

በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ ላይ የትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር)፣ የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር አብዱልበር ሸምሱ፣ የትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ ዴንጌ ቦሩ እና ሌሎች የትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ተዋናዮች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026

<p>የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...

Feb 28, 2025