የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

<p>ለምርት ዘመኑ 13 ነጥብ 4 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ግዥ ተፈጽሟል - ግብርና ሚኒስቴር</p>

Feb 8, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ጥር 30/2017(ኢዜአ)፦ ለ2017/18 የምርት ዘመን 13 ነጥብ 4 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ግዥ መፈፀሙን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ።

የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ሶፊያ ካሳ(ዶ/ር) ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት መግለጫ መንግስት ለግብርናው ዘርፍ ልዩ ትኩረት መስጠቱን ተከትሎ በዘርፉ አመርቂ ውጤት እየተመዘገበ ነው።

መንግስት ዘርፉን ለማሳደግ በትኩረት ከሚሰራባቸው ጉዳዮች አንዱ የአፈር ማዳበሪያ ግዥ መሆኑን አስታውቀዋል።

በዚህም ለ2017/18 የምርት ዘመን የሚውል የአፈር ማዳበሪያ ከጂቡቲ ወደብ ወደ ኢትዮጵያ የማጓጓዝ ስራ በከፍተኛ ትጋት እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡

በምርት ዘመኑ 24 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ግዥ ለመፈፀም ታቅዶ 13 ነጥብ 4 ሚሊዮን ኩንታል ግዥ መፈፀሙን ተናግረዋል።

የአፈር ማዳበሪያውም አምና ከነበረው አቅርቦት የአራት ሚሊዮን ኩንታል ብልጫ እንዳለውም ሚኒስትር ዴኤታዋ ገልፀዋል።

ከተገዛው 13 ነጥብ 4 ሚሊዮን ኩንታል ውስጥ 6 ነጥብ 4 ሚሊዮን ኩንታል የሚሆነው ጂቡቲ ወደብ መድረሱን በመጥቀስ አሁን ላይ ከ4 ሚሊዬዮን ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ወደ ሀገር ውስጥ መግባቱን ተናግረዋል።

የአፈር ማዳበሪያውን ከማጓጓዝ ጎን ለጎን የአርሶ አደሩን አቅም ባገናዘበ መልኩ የማስራጨት ስራ ይከናወናል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026

<p>የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...

Feb 28, 2025