የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

<p>በሀረሪ ክልል የኮሪደር ልማቱን በምሽትም ጭምር በማከናወን ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ ነው-አቶ ኦርዲን በድሪ</p>

Feb 7, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ጥር 29/2017(ኢዜአ)፦በሃረሪ ክልል የኮሪደር ልማት ስራዎችን በምሽት ጭምር በማከናወን ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ገለፁ።

ርዕሰ መስተዳድሩ በሀረር ከተማ የኮሪደር ልማት የምሽት ስራ እንቅስቃሴዎችን የመንገድ ዳር መብራቶች፤ የአባዲር ፕላዛና የአረንጓዴ ልማት ስራዎችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።


የኮሪደር ልማት ስራውን በጥራትና በፍጥነት አጠናቆ ለህብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ ትኩረት መሰጠቱን የገለፁት ርዕሰ መስተዳድሩ በተለይ ስራዎችን በምሽት ጭምር የማከናወን የስራ ባህልን በማዳበር ተጨባጭ ለውጥ እያሳየ መሆኑን ተናግረዋል።

የኮሪደር ልማቱ ከተማዋን ለኑሮ ምቹ በማድረግ የነዋሪዎችን ተጠቃሚነት ታሳቢ ባደረገ መልኩ እየተሰራ እንደሚገኝም አክለዋል።

በተለይ የሀረር ከተማን ገፅታ ከመቀየር ባለፈ ለበርካታ ወገኖች የስራ እድል በመፍጠር በኢኮኖሚ ተጠቃሚ እያደረገ እንደሚገኝ መግለጻቸውን ከክልሉ ኮሙኒኬሽን የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

የኮሪደር ልማቱ ለነዋሪውና ለቱሪስቶች የተመቸች ዘመናዊ ከተማን ለመፍጠር የሚያግዝ መሆኑን በመጠቆም ስራዎችን በፍጥነት ለማጠናቀቅ የምሽት ፈረቃ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ገልጸዋል።

በመስክ ምልከታው ላይ የክልሉ ካቢኔ አባላት ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026

<p>የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...

Feb 28, 2025