
አዲስ አበባ፤ ጥር 29/2017(ኢዜአ)፦በሃረሪ ክልል የኮሪደር ልማት ስራዎችን በምሽት ጭምር በማከናወን ተጨባጭ ለውጦች እየተመዘገቡ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ገለፁ።
ርዕሰ መስተዳድሩ በሀረር ከተማ የኮሪደር ልማት የምሽት ስራ እንቅስቃሴዎችን የመንገድ ዳር መብራቶች፤ የአባዲር ፕላዛና የአረንጓዴ ልማት ስራዎችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል።

የኮሪደር ልማት ስራውን በጥራትና በፍጥነት አጠናቆ ለህብረተሰቡ ተደራሽ ለማድረግ ትኩረት መሰጠቱን የገለፁት ርዕሰ መስተዳድሩ በተለይ ስራዎችን በምሽት ጭምር የማከናወን የስራ ባህልን በማዳበር ተጨባጭ ለውጥ እያሳየ መሆኑን ተናግረዋል።
የኮሪደር ልማቱ ከተማዋን ለኑሮ ምቹ በማድረግ የነዋሪዎችን ተጠቃሚነት ታሳቢ ባደረገ መልኩ እየተሰራ እንደሚገኝም አክለዋል።
በተለይ የሀረር ከተማን ገፅታ ከመቀየር ባለፈ ለበርካታ ወገኖች የስራ እድል በመፍጠር በኢኮኖሚ ተጠቃሚ እያደረገ እንደሚገኝ መግለጻቸውን ከክልሉ ኮሙኒኬሽን የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
የኮሪደር ልማቱ ለነዋሪውና ለቱሪስቶች የተመቸች ዘመናዊ ከተማን ለመፍጠር የሚያግዝ መሆኑን በመጠቆም ስራዎችን በፍጥነት ለማጠናቀቅ የምሽት ፈረቃ ስራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉም ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ገልጸዋል።
በመስክ ምልከታው ላይ የክልሉ ካቢኔ አባላት ተገኝተዋል።
ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...
Apr 3, 2026
ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...
Mar 31, 2026
ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...
Mar 26, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025