የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

<p>የተደረገልንን ድጋፍ እንደ መልካም እድል በመጠቀም የምግብ ዋስትናችንን ማረጋገጥ ችለናል</p>

Feb 6, 2025

IDOPRESS

ዲላ ጥር 28/2017 (ኢዜአ):- የተደረገልንን ድጋፍ እንደ መልካም እድል በመጠቀም የምግብ ዋስትናችንን ማረጋገጥ ችለናል ሲሉ የዲላ ከተማ የልማታዊ ሴፍቲኔት ተጠቃሚዎች ገለጹ።

በከተማው ላለፉት ሶስት ዓመታት በፕሮግራሙ ታቅፈው የኑሮ ደረጃቸውን ያሻሻሉ 473 የቤተሰብ አስተዳዳሪዎች የምርቃት መርሃ ግብር ተካሂዷል።

በወቅቱ የላቀ ውጤት ላስመዝገቡ ተጠቃሚዎች እውቅናና የማበረታቻ ሽልማት ተሰጥቷል።


እውቅና ካገኙት የፕሮግራሙ ተሳታፊዎች መካከል ወይዘሮ ነጻነት ግልዶ በተሰጣቸው የገንዘብ ድጋፍ በከተማ ግብርና በተለይም በእንስሳት እርባታ ተሰማርተው ለውጥ ማምጣታቸውን ጠቅሰዋል።

በአሁኑ ወቅት ከ12 በላይ የበግና የፍየል ሙክት ያላቸው ሲሆን ለገበያ በማቅረብ ኑሯቸውን ማሻሻል እንደቻሉ ጠቁመዋል።

በአካባቢ ልማት ዘርፍ ተሰማርተው ካገኙት ሳንቲም ቆጥበው በአነስተኛ ንግድ መሰማራታቸውን ያነሱት ደግሞ ሌላዋ አስተያየት ሰጭ ወይዘሮ ፀሐይ ክፍሌ ናቸው።

የንግድ ስራቸውን በማሳደግ ከ40 ሺህ ብር በላይ ተቀማጭ እንዳላቸው ጠቅሰው፤ በዚህም አራት ቤተሰቦቻቸውን ማስተዳደር እንዳስቻላቸው ጠቅሰዋል።

የዲላ ከተማ ልማታዊ ሴፍቲኔት ሥራ ፕሮግራም አስተባባሪ አቶ የኋላሸት ለማ "የሴፍቲኔት መርሃ ግብር በከተማ ዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎችን ኑሮ ከማሻሻል ባለፈ የከተማውን ልማት እያገዘ ነው" ብለዋል።

በተለይም አነስተኛ የመሠረተ ልማት ስራዎች፣ የአካባቢ ፅዳትና ውበት፣ አረንጓዴ ልማት በተሳታፊዎቹ ከሚከናወኑ ተግባራት መካከል ተጠቃሽ መሆናቸውን አስረድተው ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ጠቁመዋል።

በከተማው ላለፉት ሶስት ዓመታት በፕሮግራሙ ታቅፈው የኑሮ ደረጃቸውን ያሻሻሉ 473 የቤተሰብ አስተዳዳሪዎች ዛሬ ራስን የመቻል ሽግግር ማድረጋቸውንም ገልጸዋል።

1 ሺህ 739 በሁለተኛ ዙር ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም ፋይናንስ ተጠቃሚዎች አስፈላጊውን የክህሎት፣ የሥራ ባህልና የስራ እቅድ ተዘጋጅቶ ወደ ስራ መግባታቸውንም ተናግረዋል።

በሽግግር መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የዲላ ከተማ ምክትል ከንቲባ አቶ ታሪኩ በየነ እንዳሉት በከተማው በልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም አማካኝነት በእስካሁኑ ሂደት 10 ሺህ 183 የህብረተሰብ ክፍሎች ተጠቃሚ ሆነዋል።

በሁለተኛ ዙር የፋይናንስ ተጠቃሚ የሚሆኑ የቤተሰብ አስተዳዳሪዎችም በድጋፍ ያገኙትን ገንዘብ ለታለመለት ዓላማ በማዋል ውጤት ማስመዝገብ እንደሚገባቸው ጠቅሰዋል።

ልማታዊ ሴፍቲኔት በክልሉ የሥራና ቁጠባ ልምድን ያሳደገ መሆኑን ያነሱት ደግሞ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ከተማና መሰረተ ልማት ቢሮ የልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ኢስማኤል ታደስ ናቸው።

በክልሉ የፕሮግራሙ ተጠቃሚዎች ውጤታማ እንዲሆኑ ለማስቻል በተከናወነ ተግባርም ውጤት መመዝገቡን ጠቁመው፤ በቀጣይም ተመራቂ የፕሮጀክቱ ተጠቃሚዎችን በመደገፍና በመከታተል ለተሻለ ውጤት መስራት እንደሚገባ አሳስበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026

<p>የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...

Feb 28, 2025