የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

<p>በክልሉ ከ12 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት 158 የመስኖ ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ ነው</p>

Jan 22, 2025

IDOPRESS

ደሴ፤ ጥር 13/2017(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ከ12 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት ተመድቦ 158 የተለያዩ የመስኖ ፕሮጀክቶች እየተከናወኑ መሆኑን የክልሉ መስኖና ቆላማ አካባቢዎች ልማት ቢሮ አስታወቀ።

በደቡብ ወሎ ዞን ደሴ ዙሪያ ወረዳ ከ62 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባ የመስኖ ፕሮጀክት ዛሬ ተመርቋል።

የክልሉ መስኖና ቆላማ አካባቢዎች ልማት ቢሮ ኃላፊ ዳኝነት ፈንታ (ዶ/ር) እንደገለጹት የክልሉ መንግስት የከርስና የገጸ ምድር ውሃን በማልማት አርሶ አደሩን በመስኖ ተጠቃሚ ለማድረግ በትኩረት እየሰራ ነው።

በዚህም አሁን ላይ በክልሉ ከ12 ቢሊዮን ብር በላይ በጀት ተመድቦ የ158 የተለያዩ የመስኖ ፕሮጀክቶች በግንባታ ላይ እንደሚገኙ ገልጸዋል።

በተያዘው ዓመት 22 የመስኖ ፕሮጀክቶች ግንባታ መጠናቀቃቸውን ገልጸው፤ የ95ቱ ግንባታ ደግሞ በጀት ዓመቱ መጨረሻ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው ብለዋል።

የመስኖ ፕሮጀክቶቹ ተጠናቀው ወደ ስራ ሲገቡ ከ26 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በአዲስ መልክ በማልማት የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት የሚያሳድጉ እንደሆኑ ገልጸዋል።

በሌላ በኩል በክልሉ ከ80 ሺህ ሄክታር መሬት በላይ ማልማት የሚችሉ 110 የመስኖ ፕሮጀክቶች ዲዛይንና ጥናት እየተካሄደ መሆኑንም ገልጸዋል።

የደቡብ ወሎ ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ አሊ ይማም በበኩላቸው የዞኑን ሰላም ከማስጠበቅ ጎን ለጎን ታላላቅ የኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ፋይዳ ያላቸው ፕሮጀክቶች ግንባታ ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በዘንድሮ ዓመት ብቻ በከፍተኛ ወጪ የተሰሩ 18 የተለያዩ የመስኖ ፕሮጀክቶች ተመርቀው አገልግሎት መጀመራቸውን ጠቅሰዋል።

በደቡብ ወሎ ዞን ብቻ ከ1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ የሚገነቡ የመስኖ ፕሮጀክቶች እንዳሉ አስረድተዋል።

የደሴ ዙሪያ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጀማል መሀመድ በበኩላቸው በወረዳው የጅርቲ ወንዝ ላይ 62 ሚሊዮን ብር የተገነባው የመስኖ ፕሮጀክት ዛሬ ተመርቆ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።

ፕሮጀክቱ 200 ሄክታር የሚጠጋ መሬት በማልማት ከ700 በላይ አርሶ አደሮች በዓመት ሶስት ጊዜ በማምረት ተጠቃሚ ያደርጋል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተጠቃሚ ሆነዋል

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...

Apr 3, 2026

በምስራቅ ጎጃም ዞን ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ በመመደብ የገበያ ማረጋጋት ሥራ እየተከናወነ ነው

ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...

Mar 31, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅማችንን አሳድጓል- አምራች ኢንዱስትሪዎች

ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...

Mar 26, 2026

<p>የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ ነው</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...

Feb 28, 2025