
አዲስ አበባ፤ ጥር 13/2017(ኢዜአ)፦በ2016/17 የመኸር ምርት ዘመን ከተሰበሰበው ሰብል እስካሁን 420 ሚሊየን ኩንታል ምርት መገኘቱን የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ።
የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ መለስ መኮንን (ዶ/ር) በምርት ዘመኑ 20 ነጥብ 5 ሚሊየን ሄክታር መሬት በተለያዩ ሰብሎች መሸፈኑን አንስተው፤ ከዚህም 614 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለማግኘት ታቅዷል ብለዋል።
ከአጠቃላዩ እስካሁን 18 ነጥብ 3 ሚሊየን ሄክታር ላይ የደረሰ ሰብል መሰብሰቡን ገልጸው፥ ተሰብስቦ ከተወቃው ሰብል ደግሞ 420 ሚሊየን ኩንታል ምርት መገኘቱን ገልጸዋል።

የምርት አሰባሰብ ስራው ብክነትን በሚቀንስ መልኩ በተቀናጀ ሁኔታ በቴክኖሎጂ ታግዞ እየተካሄደ መሆኑን ሚኒስትር ዴኤታው ጠቅሰዋል።
በቀጣይም ዘግይተው የተዘሩ ሰብሎች የምርት ስብሰባም እንደሚከናወን አመላክተዋል።
በሌላ በኩል በሀገሪቱ የእርሻ ስራን ከዘር መዝራት እስከ ምርት መሰብሰብ የሚያዘምኑ ተግባራት እየጨመሩ መሆናቸውን ሚኒስትር ዴኤታው አብራርተዋል።
ዘመናዊ የእርሻ መሳሪያዎችን የአስተራረስ ስልቶች እየተተገበሩ መሆኑን ጠቅሰው፥ ለአብነትም የኩታ ገጠም እርሻ በየዓመቱ እያደገ መምጣቱን ገልጸዋል።
ለአብነትም ባለፈው የመኸር ዓመት 8 ነጥብ 6 ሚሊየን ሄክታር መሬት በኩታ ገጠም ዘዴ መታረሱን ጠቅሰው በ2016/17 ምርት ዘመን ወደ 12 ነጥብ 4 ሚሊየን ሄክታር መሬት ማደጉን ነው ያብራሩት።
ይህም የምርት ጥራትንና ምርታማነትን የሚያሳድግ ነው ብለዋል።
ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...
Apr 3, 2026
ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...
Mar 31, 2026
ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...
Mar 26, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025