
አዲስ አበባ፤ ጥር 10/2017(ኢዜአ)፡- መንግሥት ወጣቶችና ሕጻናት በቴክኖሎጂና ዲጂታላይዜሽን ቁልፍ ተዋናይ የሚሆኑበት ምቹ ምህዳር እየፈጠረ መሆኑን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ባይሳ በዳዳ (ዶ/ር) ገለጹ።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከኢትዮ ሮቦ ሮቦቲክስ የትምህርትና ውድድር ማዕከል ጋር በመተባበር በሰው ሰራሽ አስተውሎት ሲያሰለጥናቸው ለነበሩ ተማሪዎች የዕውቅና ሰጥቷል።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ባይሳ በዳዳ (ዶ/ር) መንግስት ልዩ ተሰጥኦ ያላቸውን ታዳጊዎች በማሰልጠን ለኢትዮጵያ የቴክኖሎጂና ዲጂታላይዜሽን ጉዞ ዋና ተዋናይ እንዲሆኑ ምቹ ምህዳር እየፈጠረ መሆኑን ገልጸዋል።
በዚህም በርካታ ወጣቶች በተለያዩ ዓለማት በቴክኖሎጂና በፈጠራ ተወዳዳሪ ሆነው ሀገራቸውን ማስጠራት ጀምረዋል ነው ያሉት።
መንግስት የጀመረውን ጥረት አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልፀው፤ የግሉ ዘርፍም የበኩሉን ሚና እንዲወጣ ጠይቀዋል።
የኢትዮ ሮቦ ሮበቲክስ መስራችና ዋና ስራ አስከያጅ ሰናክሪም መኮንን ስልጠናው ወጣቶች የሳይንስና ቴክኖሎጂ፣ ምህንድስና እና ሂሳብ አተገባበርን በመማር ሮቦትን እንዲቀርጹ የሚያደርግና በሮቦት ኮዲንግና እና ፕሮግራሚንግ ላይ ያተኮረ እንደሆነ ገልጸዋል።

ዕውቅና የተሰጣቸው ተማሪዎች ከዚህ ቀደም በሮቦቲከስ ፕሮግራሚንግና ኢንጅነሪንግ ሰልጥነው በቻይና ሀገር በተካሄደ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ውድድር ላይ በመሳተፍ ሶስተኛ ደረጃን ይዘው በማጠናቀቅ የሜዳሊያና የዋንጫ ተሸላሚ የነበሩ እንደሆኑ ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...
Apr 3, 2026
ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...
Mar 31, 2026
ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...
Mar 26, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025