
ጂንካ፤ ጥር 7/2017(ኢዜአ):- በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አሪ ዞን ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ከቦንድ ሽያጭ ከ26 ሚሊዮን ብር በላይ ለማሰባሰብ ታቅዶ ወደ ተግባር መገባቱን የዞኑ አስተዳደር አስታወቀ።
የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የገቢ ማሰባሰብ ንቅናቄ መርሀ ግብር ዛሬ በአሪ ዞን ጂንካ ከተማ ተጀምሯል።
የአሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብረሃም አታ በንቅናቄ መርሀ ግብሩ ላይ እንደገለፁት፤ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን ለማጠናቀቅ በዞኑ ህብረተሰቡን ያሳተፈ የሀብት አሰባሰብ ንቅናቄ ተጀምሯል።
ከጥር 7 ቀን ጀምሮ እስከ ሚያዚያ 2017 ዓ.ም ለአራት ወራት በሚቆየው የቦንድ ሽያጭ ንቅናቄ ከ26 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ለማሰባሰብ ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱን ተናግረዋል።

የዞኑ ህዝብም እንደ ወትሮው ቦንድ በመግዛትና ሌሎች ድጋፎችን በማድረግ የሀብት አሰባሰብ ስራው ውጤታማ እንዲሆን እገዛ እንዲያደርግ ጠይቀዋል።
በንቅናቄ መርሀ ግብሩ ማስጀመሪያ ላይ አስተያየታቸውን ለኢዜአ ከሰጡ የጂንካ ከተማ ነዋሪዎች መካከል አቶ ደሳለኝ ደጀኔ እንደገለፁት፤ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የኢትዮጵያ የወደፊት ተስፋ በመሆኑ ለግድቡ የሚታጠፍ እጅ የለንም ብለዋል።
የህዳሴ ግድብ የመሰረት ድንጋይ ከተቀመጠበት ጊዜ ጀምሮ ቦንድ በመግዛትና ሌሎች ድጋፎችን ሲያደርጉ መቆየታቸውን ገልጸው፤ አሁንም ቦንድ በመግዛት ተሳትፏቸውን እንደሚያጠናክሩ ገልጸዋል።
የግድቡ ግንባታ ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ ለአገልግሎት እስኪበቃ ድጋፋችን አይቋረጥም ያለው ደግሞ ወጣት ባንታየሁ አለሙ ነው።
ለግድቡ ግንባታ ማጠቃለያ የተጀመረውን የሀብት ማሰባሰብ ስራ በስኬት ለማጠናቀቅ ቦንድ በመግዛት እና ህብረተሰቡን በማስተባበር የነቃ ተሳትፎ ለማድረግ መዘጋጀቱን ተናግሯል።
የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዋንጫ በሚያዚያ ወር ወደ አሪ ዞን እንደሚደርስ የተገለፀ ሲሆን ዋንጫውን በመቀበል የሀብት አሰባሰቡ ላይ በንቃት ለመሳተፍ ዝግጅት መደረጉም ተመልክቷል።
ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...
Apr 3, 2026
ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...
Mar 31, 2026
ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...
Mar 26, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025