
አዲስ አበባ ፤ጥር 3/2017 (ኢዜአ) ፦በኢትዮጵያ ጠንካራ የካፒታል ገበያ ስርዓት ለመገንባት የሌሎች አገራትን ተሞክሮ በራስ አውድ መተግበር እንደሚገባ የአፍሪካ የሰነደ ሙዓለ-ንዋይ ገበያ ማህበር ፕሬዝዳንት ሰልስቲያን ፔሪ ገለፁ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የኢትዮጵያ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያን ትናንት በይፋ አስጀምረዋል።
በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩ በተደረገ የፓናል ውይይት ላይ የአፍሪካ የሰነደ ሙዓለ-ንዋይ ገበያ ማህበር ፕሬዝዳንት ሰልስቲያን ፔሪ እንዳሉት በኢትዮጵያ የህግ ማዕቀፍ ተዘጋጅቶ ስራው መጀመሩ በስኬት የሚነሳ ነው።
ይህም በአገሪቱ የሰነደ ሙዓለ ንዋይን ለመጀመር የሚያስችል መሆኑን ጠቁመዋል።
በአለም የካፒታል ገበያ ሳይኖር ውጤታማ ኢኮኖሚ መገንባት አለመቻሉን አንስተው የተለያዩ ልምዶችን መቀመርና ከሌሎች አገራት መማር እንደሚቻል ተናግረዋል።
በአፍሪካ አብዛኛው አገራት አነስተኛ ገበያ ያላቸው መሆኑን አንስተው ሆኖም ትልቅ ገበያን ለመመስረት ጠንካራ የካፒታል ገበያ ከገነቡት ልምድን መውሰድ ይገባል ብለዋል።

በኢትዮጵያም ስኬታማ ከሆኑ አገራት ጥሩ ተሞክሮን በመቅሰም ለራስ በሚጠቅም አውድ መተግበር እንደሚገባም አስረድተዋል።
ከጠንካራ ህግና መመሪያዎች በተጨማሪ የካፒታል ገበያ ላይ እውቀት ያላቸው ባለሙያዎች እንዲበራከቱና የህብረተሰቡን የቁጠባ መጠን ማሳደግ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸው፤ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራ እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል።
በኢትዮጵያ የካፒታል ገበያውን የሚቆጣጠሩ አካላት በተቀናጀ አግባብ መስራት እንዳለባቸውም ገልፀዋል።
በአፍሪካ ከጥቂት አገራት በስተቀር የባንኮች ተቀማጭ ገንዘብ በቂ አለመሆኑን ጠቅሰው፤ ለዚህም የሰነደ ሙዓለ-ንዋይ ግብይት ወሳኝ መሆኑን አስረድተዋል።
የቁጠባ መጠንን ማሳደግና ፕራይቬታይዜሽንን ማጠናከር ለካፒታል ገበያ አስፈላጊ መሆኑንም ጠቁመዋል።
የአገር ውስጥ ኢንቨስተሮች ገበያውን በሚገባ ከደገፉ በአገር ውስጥ አቅም ኢኮኖሚውን ማጠናከር እንደሚቻልም ነው የተናገሩት።
ኢትዮጵያ በአፍሪካ ትልቅ ምጣኔ ሃብት ያላት አገር በመሆኗ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ የሆነ ኢኮኖሚ ለመገንባት የተጠናከረ የካፒታል ገበያ እንደሚያስፈልጋት አስረድተዋል።
ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...
Apr 3, 2026
ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...
Mar 31, 2026
ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...
Mar 26, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025