
ሆሳዕና፤ ታኅሣሥ 26/2017(ኢዜአ):- በግብርና ዘርፍ የሚከናወኑ የጥናትና ምርምር ስራዎች ለውጤት እንዲበቁ የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ እንዲጠናከር የኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ጠየቀ።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በግብርናው ዘርፍ ያሉ ዕድሎችንና ማነቆዎችን ለመለየት የተከናወኑ ጥናቶች ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ በሆሳዕና ከተማ ዛሬ ተካሄዷል።
በኢንስቲትዩቱ የምግብ ማጠናከሪያ ፕሮግራም የምርምር ዘርፍ ዳይሬክተር ንጉሴ ዳና (ዶ/ር) እንዳሉት ኢንስቲትዩቱ በስምንት የምርምር ማዕከላት የግብርናውን ዘርፍ የሚያግዙ የጥናትና ምርምር ውጤቶች እንዲፈልቁና ተደራሽ እንዲሆኑ እያደረገ ነው።
በተለይም ቴክኖሎጂን የማስረጽ ስራ ውጤት እየተገኘበት መሆኑን ጠቅሰው እነዚህን ጅምር ስራዎች በመደገፍ ረገድ ባለድርሻ አካላት መረባረብ አለባቸው ብለዋል።
ኢንስቲትዩቱ ለግብርናው ዘርፍ ማነቆ የሆኑ ችግሮችን መፍታት የሚያስችሉ የምርምር ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን የገለጹት ዳይሬክተሩ የቴክኖሎጂዎች አቅርቦትን በማመቻቸት፣ በማስፋትና በማስተዋወቅ ለተጠቃሚው እንዲደርስ የሁሉም ርብርብ ያስፈልጋል ብለዋል።
በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የገጠር ክላስተር አስተባባሪና የግብርና ቢሮ ኃላፊ አቶ ኡስማን ሱሩር በበኩላቸው በክልሉ በምርምር የተገኙ የግብርና ተክኖሎጂዎች ተደራሽነት ትኩረት ማግኘቱን ገልጸዋል።
የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ፣ የግብርና ምርቶችን በአይነትና በጥራት ማምረትና ዘርፉ ለዜጎች የስራ እድል መፍጠሪያ እንዲሆን ትኩረት ተሰጥቷል ብለዋል።
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ምርምር ኢንቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ፀጋዬ ተረፈ፣ በክልሉ የግብርና ልማትን የሚያግዙ የጥናትና ምርምር ስራዎች በትብብር እየተሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል።
በዚህም በተቋሙ ስር የሚገኙ የምርምር ማዕከላትንና ንዑስ የምርምር ጣቢያዎችን በማቀናጀት በርካታ የጥናት ስራዎች መከናወናቸውን አስረድተዋል።
በመርሐ ግብሩ ላይ የክልሉ ከፍተኛ አመራር አባላት፣ የዞንና የልዩ ወረዳ ግብርና መምሪያ ኃላፊዎች፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አመራር አባላትና ሌሎች እንግዶች ተሳትፈዋል።
ሀዋሳ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፡- የሀዋሳ ከተማን ፈጣን እድገት የሚያሳልጡ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳ...
May 20, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026