
ደሴ፤ ታኅሣሥ 15/2017 (ኢዜአ)፦ በአገር አቀፍ ደረጃ ከ2 ነጥብ 4 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት በበጋ መስኖ ስንዴ ልማት መሸፈኑን የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ መለስ መኮንን(ዶ/ር) ገለጹ፡፡
የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ መለስ መኮንን(ዶ/ር)ን ጨምሮ ከፍተኛ የፌዴራልና የክልል የመንግስት የስራ ሃላፊዎች በተገኙበት በደቡብ ወሎ ዞን ቃሉ ወረዳ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ተጀምሯል።
ሚኒስትር ዴኤታው በዚሁ ወቅት እንዳሉት የበጋ መስኖ ስንዴ ምርታማነትን በማሳደግ የዜጎችን የምግብ ዋስትና ከማረጋገጥ ባለፈ ምርት በስፋት ለገበያ ለማቅረብ እየተሰራ ነው፡፡
የውሃ አማራጮችን በመጠቀም ለበጋ መስኖ ስንዴ ልማት ትኩረት መስጠቱን ጠቁመው፤ በዘንድሮው የበጋ ወራት ከ4 ነጥብ 2 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በላይ በስንዴ ለማልማት እየተሰራ ይገኛል፡፡
እስካሁን በተደረገ እንቅስቃሴም ከ2 ነጥብ 4 ሚሊዮን ሄክታር የሚበልጥ መሬት በስንዴ ዘር መሸፈን እንደተቻለ ነው የተናገሩት።
ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያግዙ ማዳበሪያን ጨምሮ ሌሎች ግብዓቶችን በበቂ መጠን እያቀረበ እንደሚገኝም ገልጸዋል፡፡
በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የአማራ ክልል ገጠር ልማት ዘርፍ አስተባባሪና ግብርና ቢሮ ኃላፊ ድረስ ሳህሉ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ የበጋ መስኖ ስንዴ ልማትን ምርታማነት ለማሳደግ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡
በዚህም 254 ሺህ ሄክታር መሬት በበጋ መስኖ ስንዴ በማልማት ከ9 ነጥብ 4 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ መታቀዱን ገልፀዋል፡፡
እስካሁን ከ120 ሺህ ሄክታር የሚበልጥ መሬት በዘር መሸፈኑን ጠቁመዋል።
በክልሉ በተሻሻለ አሰራር ምርታማነትን በማሳደግ በምግብ ራስን ከመቻል ባለፈ በቂ ምርት ለገበያ እንዲቀርብ ጭምር እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡
ጎንደር፤ መጋቢት 24/2018( ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ከ239 ሺ በላይ የህብረተሰብ ክፍሎች በከተሞች የምግብ ዋስትና ስትራቴጂ ተ...
Apr 3, 2026
ደብረ ማርቆስ፤ መጋቢት 21/2018 (ኢዜአ):-በምስራቅ ጎጃም ዞን ገበያውን ለማረጋጋት ከ169 ሚሊዮን ብር በላይ ተመድቦ እየተሰራ መሆኑን የዞኑ የህብረት ሥራ...
Mar 31, 2026
ሀዋሳ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፡- የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የማምረት አቅም በማሳደግ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ጉልህ ሚና እያበረከተ መሆኑን አምራ...
Mar 26, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ)፦ የቁልፍ መሰረተ ልማቶች ጥበቃ አዋጅን ሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስ...
Feb 28, 2025