የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በክልሉ የአፈር ማዳበሪያ ከአካባቢው የአፈር ሁኔታ ጋር በማስማማት መቅረብ መጀመሩ በምርት ላይ ውጤት እያስገኘ ነው

May 15, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሰመራ፤ ግንቦት 7/2018 (ኢዜአ)፦ በአፋር ክልል የአፈር ማዳበሪያን ከአካባቢው የአፈር ሁኔታ ጋር በማስማማት መቅረብ መጀመሩ በምርት ላይ ውጤት እያስገኘ መሆኑን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ ገለፀ።

ለዘመናት በከብት እርባታ የሚታወቀው የአፋር ህዝብ፣ ከለውጡ ዓመታት ወዲህ ወደ መስኖና ቋሚ ግብርና በስፋት እየተሸጋገረ ይገኛል።

የአፈር ለምነትን ለማሻሻልና የግብርና ስራውን የባህላዊ አሰራር ተጽዕኖ በማውጣት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የአፈር ማዳበሪያ አጠቃቀም በክልሉ እየተለመደ መጥቷል።

በክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ቢሮ የእርሻ ኢንቨስትመንትና ግብአት ዘርፍ ምክትል ኀላፊ አቶ ሃሩን ዓሊ እንደተናገሩት፤የአፈር ማዳበሪያውን ከአካባቢው የአፈር ሁኔታ ጋር በማስማማት ማቅረብ መጀመሩ ምርትን በማሳደግ ላይ ትልቅ መሻሻል አሳይቷል።

በበጀት ዓመቱ 50 ሺህ ኩንታልየአፈር ማዳበሪያ ለማስገባት ታቅዶ ወደ ስራ የተገባ ሲሆን በእስካሁኑ እንቅስቃሴ 48 ሺህ 800 ኩንታል ቀርቦ በጋሊኮማና ደንከሊያ ዮኒየኖች አማካኝነት በመሠራጨት ላይ መሆኑም ተመላክቷል።

በክልሉ የአፈር ማዳበሪያ አጠቃቀም በይፋ መጀመሩን ተከትሎ፣ በተለያዩ የአዝዕርት፣ የፍራፍሬና የአትክልት ምርቶች ላይ ከፍተኛ የሆነ የምርት ጭማሪ መታየቱን ገልጸዋል።

ይህ ስኬትም ባለፉት የለውጥ ዓመታት በዘርፉ የተከናወኑ የለውጥ ስራዎችና የተመዘገቡ መሻሻሎች ውጤት መሆኑን ገልጸዋል።

ሀገራዊ ለውጡን ተከትሎ በአፋር ክልል የተከናወኑ የግብርና ስራዎች፣ በረሃማ አካባቢዎችን ማልማት እንደማይቻል ይታመንበት የነበረውን የተዛባ ትርክት የቀየሩና ማንኛውንም ሰብል ማምረት እንደሚቻል በተግባር ያረጋገጡ መሆናቸውን ተናግረዋል።

የግብዓት አቅርቦቱ ብቻውን ስኬታማ ሊሆን እንደማይችል የጠቀሱት አቶ ሃሩን፣ ማዳበሪያው በአግባቡና በሳይንሳዊ መንገድ ጥቅም ላይ እንዲውል የእያንዳንዱ አርሶ አደር ማሳ በባለሙያዎች እንዲታገዝ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል።

ይህም አርሶ አደሩና አርብቶ አደሩ ከቴክኖሎጂው ተገቢውን ውጤት እንዲያገኝና የምርት ብክነትን ለመቀነስ ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን አብራርተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ ነው-ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ

ሰመራ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ መሆናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

May 21, 2026

በከተማው በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የተስተዋለውን ክፍተት ለማረም በተሰራው ሥራ ለውጥ መጥቷል

ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...

Apr 30, 2026

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና እድገትን በምርምር ማገዝ አለባቸው

ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...

Apr 30, 2026

የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...

Apr 29, 2026