🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 6/2018(ኢዜአ)፡-የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዘመናዊ አውሮፕላኖችን በመግዛት፣ በማንቀሳቀስና በመጠገን በአፍሪካ ቀዳሚ መሆኑን ዋና ሥራ አስፈፃሚው አቶ መስፍን ጣሰው ገለጹ።
አየር መንገዱ 80ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን ምክንያት በማድረግ ዛሬ የመሬት ላይ አውሮፕላን ትዕይንት (Static Air Show) አካሂዷል።
አውሮፕላኖች ለሕዝብ ዕይታ የሚቀርቡበትን ትዕይንት የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው ከፍተውታል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ አየር መንገዱ 80ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን ለማክበር የተለያዩ መርሃ ግብሮችን በማከናወን ላይ ይገኛል።
ዛሬ የቀረበው የመሬት ላይ አውሮፕላን ትዕይንትም የዚሁ ክብረ በዓል አካል መሆኑን ገልጸዋል።
ይህ መርሃ ግብር አየር መንገዱ በየዓመቱ 21 ሚሊዮን መንገደኞችን እና 850 ሺህ ቶን ጭነት ለማጓጓዝ የሚጠቀምባቸውን ዘመናዊ አውሮፕላኖች ለማህበረሰቡ ያስተዋወቀበት መሆኑን ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሁል ጊዜም ዘመናዊ የቴክኖሎጂ ውጤቶች የሆኑ አውሮፕላኖችን በመግዛት፣ በማንቀሳቀስ እና በመጠገን ረገድ በአፍሪካ ቀዳሚ መሆኑንም አረጋግጠዋል።
ይህም አየር መንገዱን በአህጉሪቷ እጅግ ስኬታማ፤ በዓለም አቀፍ ደረጃም ዘመናዊና አዳዲስ አውሮፕላን ስብስብ (Young Fleet) ያለው ተወዳዳሪ አየር መንገድ እንዳደረገው ገልጸዋል።
በአሁኑ ወቅት አየር መንገዱ 147 አውሮፕላኖች እንዳሉት የገለጹት ዋና ሥራ አስፈፃሚው፤ አሁን ላይ እያደገ ከመጣው ፍላጎት አኳያ ቁጥሩ በቂ አለመሆኑን አስረድተዋል።
ለዚህም ይረዳ ዘንድ ከቦይንግ እና ኤርባስ ኩባንያዎች ከ100 በላይ አውሮፕላኖች መታዘዛቸውን ጠቁመዋል።
አየር መንገዱ በአምስት አህጉራት፣ በ82 ሀገራት እና በ140 መዳረሻዎች በረራ በማድረግ ሰዎችን በማገናኘትና ባህላዊ ትስስር በመፍጠር ረገድ አስደናቂ ሚና እየተወጣ እንደሚገኝም አብራርተዋል።
አየር መንገዱ ላለፉት 80 ዓመታት ዘመናዊ አውሮፕላኖችን በመጠቀም በአፍሪካ ሰማይ ላይ ቀዳሚ መሆኑን አመልክተው፤ ሀገራትን በማቀራረብና በዓለም አቀፍ የባህልና የንግድ ልውውጥ ረገድ ወሳኝ ሚና ሲጫወት መቆየቱን ዋና ሥራ አስፈፃሚው ገልጸዋል።
ሰመራ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ መሆናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
May 21, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026