🔇Unmute
አዳማ፤ ግንቦት 4/2018(ኢዜአ)፦ በክልሉ በመጪው ክረምት በሚከናወነው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ከ10 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በአቮካዶ ተክል እንደሚሸፈን የኦሮሚያ ግብርና ቢሮ ገለፀ።
በቢሮው የአትክልትና ፍራፍሬ ዘርፍ ኃላፊ ሙሐመድሳኒ አሚን ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በክልሉ የተሻሻሉ የአቮካዶ ዝርያዎችን ለአርሶ አደሩ ተደራሽ በማድረግ የአቮካዶ ልማት ኢኒሼቲቭን ውጤታማ ለማድረግ እየተሰራ ነው።
በመጪው ክረምት ለሚከናወነው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብርም አስር አይነት የተለያዩ የፍራፍሬ ችግኞች ተዘጋጅቷል ነው ያሉት።
በተለይም አቮካዶ፣ ሙዝ፣ ዘይቱን፣ ፓፓያ፣ ግሽጣ፣ ብርቱካን፣ አፕል፣ ሎሚና ሌሎች የፍራፍሬ ችግኞች በስፋት መዘጋጀታቸውን ጨምረው ገልፀዋል።
በክልሉ የአቮካዶ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተሻሻሉና ከፍተኛ ምርት የሚሰጡ ዝርያዎችን በማዳቀል የችግኝ ዝግጅት ላይ በስፋት እየተሰራ ይገኛል ነው ያሉት።
በክልሉ እስካሁን ከ80 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በመደበኛና በተሻሻሉ የአቮካዶ ችግኞች መሸፈኑንም ገልጸዋል።
በተለይ ለወጪ ንግድ የሚሆን አቮካዶ ልማትን ለማሳደግና ምርትና ምርታማነቱን ማሳደግ ለሚያስችሉ ስራዎች ትኩረት መሰጠቱን ጠቁመው በሁሉም የክልሉ ዞኖች፣ ከተሞችና ወረዳዎች በክላስተርና በመደበኛነት እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።
ሰመራ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ መሆናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
May 21, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026