የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

ከጉጂ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ18 ሺህ ቶን በላይ የቡና ምርት ለማእከላዊ ገበያ ቀርቧል

May 12, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዶላ፤ ግንቦት 4/2018(ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን በዘንድሮው ዓመት ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ18 ሺህ ቶን በላይ ጥራቱን የጠበቀ የቡና ምርት ለማእከላዊ ገበያ መቅረቡን የዞኑ ንግድ ጽህፈት ቤት ገለጸ።

ልዩ ጣዕም ያለውን ቡና በማምረት ለዓለም ገበያ በማቅረብ ላይ ከሚገኙ የኢትዮጵያ አካባቢዎች አንዱ የጉጂ ዞን ነው።

በዞኑ አብዛኛው የቡና ልማት በተፈጥሮ ደኖች ጥላ ስር የሚከናወን በመሆኑ፣ ምርቱ ተፈጥሯዊ (Organic) ይዘቱን ሳይለቅ እንዲያድግ ይረዳዋል።

በዞኑ ንግድ ጽህፈት ቤት የእቅድና በጀት ባለሙያ ደረሰ ደንቆ ለኢዜአ እንደገለጹት በበጀት ዓመቱ ከዞኑ ከ75 ሺህ ቶን በላይ የቡና ምርት ለማእከላዊ ገበያ ለማቅረብ ታቅዶ እየተሰራ ይገኛል።

በዞኑ የሚገኙ 36 የቡና ምርት አቅራቢዎች ምርቱን በብዛትና በጥራት እያዘጋጁ ለማእከላዊ ገበያ በማቅረብ ላይ እንደሚገኙም ጠቅሰዋል።

በዚህም በበጀት ዓመቱ ባለፉት ዘጠኝ ወራት 18 ሺህ 682 ቶን ጥራቱንና ደረጃውን የጠበቀ ታጥቦ የተቀሸረ ደረቅ የቡና ምርት ለማእከላዊ ገበያ መቅረቡን ገልጸዋል።

ዘንድሮ ለገበያ ለማቅረብ የታቀደው ምርት ከዓምና ጋር ሲነጻጸር እድገት ማሳየቱንም ተናግረዋል።

በሀገር አቀፍ ደረጃ ለመጀመሪያ ጊዜ በዞኑ የቡና ጣእም ቅምሻ ማእከል መቋቋሙን ገልጸው፤ ማዕከሉ የቡና ምርት ጥራትና ብዛትን በመጨመር በአምራቾች ዘንድ መነሳሳት መፍጠር መቻሉን አንስተዋል።

በዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት የቡናና ሻይ ልማት ባለሙያ አቶ ብርሃኑ ፈይሳ በበኩላቸው የቡና ልማቱን ለማስፋት የተሻለ ምርት የሚሰጡ የተሻሻሉ የቡና ዝርያዎች ለአርሶ አደሩ እየቀረበ ይገኛል።

በዚህ ዓመት ከአንድ ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ መታቀዱን ጠቅሰው፣ በልማቱም ከ108 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች በመሳተፍ ተጠቃሚ መሆናቸውን አስታውቀዋል።

የአዶላ ከተማ ነዋሪና የቡና አምራች አቶ ጌታቸው ጎልጃ በሰጡት አስተያየት፣ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በተሻሻለው የቡና ልማትና ግብይት ተጠቃሚ መሆናቸውን አስታውቀዋል።

የቡና ጣእምና የቅምሻ ማእከል በአካባቢያቸው መቋቋሙን ተከትሎ የቡና ምርቱን በብዛት እና በጥራት በማምረትና ለገበያ በማቅረብ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ እየሰሩ መሆኑንም አመልክተዋል።

ሌላው የቡና አቅራቢ የሆኑት አቶ ኤልያስ ሰንጋጎ ከዘርፉ ገቢያቸውን ለማሳደግ ለምርት ጥራት ትኩረት መስጠታቸውን አስታውቀዋል።

የጉጂ ዞን ከ377 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በቡና ተከል መሸፈኑ ታውቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ ነው-ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ

ሰመራ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ መሆናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

May 21, 2026

በከተማው በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የተስተዋለውን ክፍተት ለማረም በተሰራው ሥራ ለውጥ መጥቷል

ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...

Apr 30, 2026

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና እድገትን በምርምር ማገዝ አለባቸው

ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...

Apr 30, 2026

የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...

Apr 29, 2026