የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የሀዋሳ ሐይቅ ዳርቻን በማልማት የቱሪዝም ማዕከል የማድረጉ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል

May 7, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሀዋሳ፤ ሚያዚያ28/2018(ኢዜአ)፦ የሀዋሳ ሐይቅ ዳርቻን በማልማትና ከአካባቢው መስህቦች ጋር በማስተሳሳር ሀይቁን የቱሪዝም ማዕከል የማድረጉ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የሃዋሳ ከተማ ከንቲባ ጥራቱ በየነ ገለጹ።

የሀዋሳ ሀይቅ ዳርቻ ልማት የዲዛይን ሥራ ተጠናቅቆ ዛሬ ለህዝብ ይፋ ተደርጓል።

ከንቲባው በዚህ ወቅት እንደገለጹት የሀዋሳ ሀይቅ ዳርቻ ልማት ሀይቁን ለትውልድ በሚተርፍ መልኩ አልምቶ ጥቅም ላይ ለማዋል የሚያስችል መሆኑንናይፋ የተደረገው ዲዛይን በሀይቁ ላይ የሚሰሩ የልማት ሥራዎችን አካቶ የያዘ መሆኑን ተናግረዋል።


ከጥቁር ውሃ እስከ ታቦር ተራራ ድረስ የሚለማውና 12 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው የሀዋሳ ሀይቅ ዳርቻ ልማት ከተማዋን በሀገር አቀፍ ደረጃ ካሉ ከተሞች ጋር ተወዳዳሪና ተመራጭ እንድትሆን ያደርጋታል ብለዋል።

ከተማዋ በርካታ የተፈጥሮ ሀብቶች ባለቤት ናት ያሉት ከንቲባው ሀይቁን በአካባቢው ካለው ታቦር ተራራ፣ ፍል ውሀዎች፣ ፏፏቴዎችና ከወንዶ ገነት ጋር በማስተሳሰር አልምቶ የቱሪስት ማዕከል ለማድረግ ይሰራል ነው ያሉት።

በሀይቅ ዳርቻ ልማቱ የጥቁር ውሀ አካባቢ፣ በተለምዶ ፍቅር ሀይቅ ተብሎ የሚጠራው የመዝናኛ ስፍራ፣ የሀዋሳ አሳ ገበያ እና አሞራ ገደል አካባቢ ተካትተው አብረው ይለማሉ ብለዋል።

የሀይቅ ዳር ልማት ሥራው የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የማማከር አገልግሎት በመስጠት እየሰራ መሆኑም ተጠቁሟል።

ዲዛይኑን ይፋ ለማድረግ በተዘጋጀ መርሀ ግብር የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ፣ የክልሉ መንግስት ዋና ተጠሪ አብርሃም ማርሻሎ፣ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የትምህርት ቢሮ ሀላፊ በየነ በራሳን ጨምሮ ሌሎች የክልሉና የከተማዋ የመንግስት የሥራ ሃላፊዎች እና ባለሀብቶች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ ነው-ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ

ሰመራ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ መሆናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

May 21, 2026

በከተማው በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የተስተዋለውን ክፍተት ለማረም በተሰራው ሥራ ለውጥ መጥቷል

ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...

Apr 30, 2026

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና እድገትን በምርምር ማገዝ አለባቸው

ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...

Apr 30, 2026

የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...

Apr 29, 2026