የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

በምስራቅ ጎጃም ዞን አሲዳማ አፈርን በኖራ በማከም ምርታማነትን ለማሳደግ ትኩረት ተደርጓል

May 6, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ደብረ ማርቆስ ፤ ሚያዝያ 27/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን አሲዳማ አፈርን በኖራ በማከም ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን የዞኑ ግብርና መምሪያ አስታወቀ።

የመምሪያው ሃላፊ አቶ ጥላሁን ንጋቱ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በመጪው መኸር ምርትና ምርታማነትን በሁሉም አማራጭ በማሳደግ በምግብ ራስን ለመቻል ርብርብ እየተደረገ ነው።


በዚህም ከ46 ሺህ ሄክታር በላይ በአሲድ የተጠቃ መሬትን በኖራ በማከም ቀድሞ ወደ ነበረበት ምርታማነት ለመመለስ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

በኖራ አቅርቦት ዙሪያ ከአቅራቢ ድርጅቶች ጋር በመነጋገር በፍጥነት ለአርሶ አደሩ ለማድረስ እየተሰራ መሆኑን የገለጹ ሲሆን እስካሁን ከ3ሺህ ኩንታል በላይ ኖራ ለአርሶ አደሩ መሰራጨቱን ተናግረዋል።

በቀጣይ ወራትም አስፈላጊውን መጠን ኖራ በማቅረብ አሲዳማ የሆነውን አፈር የማከሙ ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል።

በመኸር ምርቱ የታቀደውን የምርት ጭማሪ ለማስመዝገብም መሬትን በኖራ ከማከም ባሻገር አዳዲስ አሰራሮችንና ቴክኖሎጂዎችን መጠቀም ላይ በማተኮር እየተሰራ ነው ብለዋል።


በዞኑ የማቻከል ወረዳ የቅዳማን ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ባየልኝ ሙላት እንደገለጹት በአሲድ የተጠቃውን አንድ ሄክታር ማሳቸውን በኖራ በማከም ዘር እየዘሩ ነው።

በኖራ አክመው ከሚዘሩት ሰብል ከአምስት ኩንታል በላይ የምርት ጭማሪ እንዳገኙ ጠቁመው ያገኙትን ጥቅም ለማሳደግም ዘንድሮ ከ30 ኩንታል በላይ ኖራ ማሳቸው ላይ መበተናቸውን ተናግረዋል።

በአነደድ ወረዳ የጉዳለማ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ጊዜአለው አግደውም ማሳቸውን በኖራ በማከም ለምነቱ እንዲመለስ እያደረጉ መሆኑን ገልጸዋል።

አሁን ላይም ከግማሽ ሄክታር በላይ ማሳቸው ላይ ኖራ በመበተን ደጋግመው ማረሳቸውን ጠቁመው በቀጣይም ከዘሩ ጋር ቀላቅለው በመዝራት ምርታማነታቸውን ለማሳደግ እንደሚሰሩም አመልክተዋል።

በመጪው የመኸር ምርት ከ660 ሺህ ሄክታር በላይ መሬትን በተለያዩ ሰብሎች በማልማት ከ26 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለማምረት ታቅዶ ወደ ስራ መገባቱ ተመልክቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ ነው-ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ

ሰመራ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ መሆናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

May 21, 2026

በከተማው በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የተስተዋለውን ክፍተት ለማረም በተሰራው ሥራ ለውጥ መጥቷል

ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...

Apr 30, 2026

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና እድገትን በምርምር ማገዝ አለባቸው

ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...

Apr 30, 2026

የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...

Apr 29, 2026