የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
የአፍሪካ ህብረት

የቅርስ ጥበቃ እና ልማት ለኢኮኖሚ ዕድገት የሚያበረክተው ሚና አድጓል

Apr 22, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፡- በኢትዮጵያ ለቅርስ ጥበቃና ልማት ሥራ በተሰጠው ልዩ ትኩረት ዘርፉ ለሀገራዊ የኢኮኖሚ ዕድገት የሚያበረክተው ድርሻ ማደጉን የቱሪዝም ሚኒስትር ዴዔታ እንደገና አበበ (ዶ/ር) ገለጹ።


3ኛው የቅርስ ምርምር ጉባዔ የኢትዮጵያ ቅርስ ምርምር በዲጂታል ዘመን በሚል መሪ ሐሳብ መካሄድ ጀምሯል።

ሚኒስትር ዴዔታው በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ የለውጡ መንግሥት በቅርስ ጥበቃና ልማት ሥራን በተመለከተ ልዩ ትኩረት በመስጠቱ በርካታ ተግባራት ተከናውነዋል።


ቅርሶች የውጭ ምንዛሪን በማስገኘት፣ የሥራ ዕድል በመፍጠር እንዲሁም ለአርኪዎሎጂስቶችና ለታሪክ ተመራማሪዎች የማይነጥፍ የመረጃ ምንጭ ሆነው እያገለገሉ እንደሚገኙ አብራርተዋል።

ቅርሶች ተጠብቀው ከትውልድ ወደ ትውልድ እንዲሸጋገሩ የማድረግ፣ የቅርስ አያያዝንና አጠቃቀምን የማዘመን ሥራ ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባም አስገንዝበዋል።


የቅርስ ጥበቃና ልማት ሥራው ዲጂታላይዝ እየተደረገ ነው ያሉት ደግሞ የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር አበባው አያሌው (ረ/ፕ) ናቸው።


ጉባዔው በቅርስ ልማት ዘርፍ ያሉ ተግዳሮቶችን መርምሮ መፍትሔ ለመስጠትና አዳዲስ ዕውቀቶችን ለመለዋወጥ የሚያስችል መሆኑንም ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ ነው-ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ

ሰመራ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ መሆናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

May 21, 2026

በከተማው በትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የተስተዋለውን ክፍተት ለማረም በተሰራው ሥራ ለውጥ መጥቷል

ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...

Apr 30, 2026

ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ቀጣናዊ ዘላቂ ሰላምና እድገትን በምርምር ማገዝ አለባቸው

ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...

Apr 30, 2026

የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ ነው 

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...

Apr 29, 2026