🔇Unmute
ጅግጅጋ፤ መጋቢት 25/2018(ኢዜአ)፦ በሶማሌ ክልል የነዳጅ ግብይትን ህጋዊነት በመቆጣጠር የትራንስፖርት እንቅስቃሴን ለማሳለጥ በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ንግድና ትራንስፖርት ቢሮ ገለጸ።
የሶማሌ ክልል ንግድና ትራንስፖርት ቢሮ ሃላፊ አቶ አብዱልሀኪም ሼክ ሀሰን በሰጡት መግለጫ በመካካለኛው ምስራቅ የተከሰተውን አለመረጋጋት ተከትሎ የገጠመው የነዳጅ ግብይትና አቅርቦት ጫና በህብረተሰቡ ላይ ተጽዕኖ እንዳያደርስ ጥብቅ ቁጥጥር መደረጉን ገልጸዋል።
ለተግባራዊነቱም የቅድሚያ ቅድሚያ ነዳጅ ለሚያስፈልጋቸው ተሽከርካሪዎች፣ የኤክስፖርት ድርጅቶች፣ የመንግሥትና የግል ፕሮጀክቶች፣ የገቢና ወጪ ንግድን ጨምሮ መሠረታዊ የፍጆታ ምርቶችን የሚያጓጉዙ ተሽከርካሪዎች ተደራሽ መደረጉን አንስተዋል።
ከዚህ ባለፈም ህገ-ወጥ የነዳጅ ግብይትን ለመቆጣጠር የክልሉ የጸጥታ ተቋማት ከፌዴራል ፖሊስና ከጉምሩክ ኮሚሽን ጋር በቅንጅት እየተሠራ ነው ብለዋል።
በዚህም ህገ-ወጥ የነዳጅ ዝውውርን ለመግታት በተደረገው ጥረት 3ሺህ 500 ሊትር ነዳጅ ከሰሞኑ በቁጥጥር ስር መዋሉን ገልጸዋል።
ህብረተሰቡ ህገ-ወጥ የነዳጅ ዝውውርን ለመቆጣጠር በሚደረገው ቅንጅታዊ ስራ ያለውን ተሳትፎ እንዲያጠናክርም ሃላፊው ጠይቀዋል።
በክልሉ አዲሱ የነዳጅ ጭማሪ ታሪፍ መደረጉንና ህብረተሰቡ ነዳጅን በቁጠባ እንዲጠቀም የግንዛቤ ስራ እየተካሄደ መሆኑንም ጠቁመዋል።
ህብረተሰቡ ሌሎች ታዳሽ ሀይልን በመጠቀምና አላስፈላጊ ጉዞ በመቀነስ የነዳጅ ቁጠባውን ተግባራዊ እንዲያደርግም መክረዋል።
ሰመራ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦በአፋር ክልል ለህብረተሰቡ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ የሚሰጡ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት እየበቁ መሆናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
May 21, 2026
ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዝያ 21/2018 (ኢዜአ)፦ በወላይታ ሶዶ ከተማ ከነዳጅ እጥረት ጋር በተያያዘ በህዝብ የትራንስፖርት አገልግሎት ላይ የነበረውን ክፍተት ለማረም...
Apr 30, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 21/2018(ኢዜአ)፦ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የምርምር ሥራዎቻቸውን ከቀጣናዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር በማስተሳሰር ዘላቂ ሰላምና የጋራ እድገት ለ...
Apr 30, 2026
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የትራንስፖርት አገልግሎትን ከነዳጅ ጥገኝነት ለማላቀቅ ተግባራዊ የተደረጉ ስልቶች ተጨባጭ ውጤት እያመጡ መሆኑን የትራን...
Apr 29, 2026