🔇Unmute
ጅግጅጋ፤ መጋቢት 25/2018(ኢዜአ)፦ በሶማሌ ክልል የነዳጅ ግብይትን ህጋዊነት በመቆጣጠር የትራንስፖርት እንቅስቃሴን ለማሳለጥ በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ንግድና ትራንስፖርት ቢሮ ገለጸ።
የሶማሌ ክልል ንግድና ትራንስፖርት ቢሮ ሃላፊ አቶ አብዱልሀኪም ሼክ ሀሰን በሰጡት መግለጫ በመካካለኛው ምስራቅ የተከሰተውን አለመረጋጋት ተከትሎ የገጠመው የነዳጅ ግብይትና አቅርቦት ጫና በህብረተሰቡ ላይ ተጽዕኖ እንዳያደርስ ጥብቅ ቁጥጥር መደረጉን ገልጸዋል።
ለተግባራዊነቱም የቅድሚያ ቅድሚያ ነዳጅ ለሚያስፈልጋቸው ተሽከርካሪዎች፣ የኤክስፖርት ድርጅቶች፣ የመንግሥትና የግል ፕሮጀክቶች፣ የገቢና ወጪ ንግድን ጨምሮ መሠረታዊ የፍጆታ ምርቶችን የሚያጓጉዙ ተሽከርካሪዎች ተደራሽ መደረጉን አንስተዋል።
ከዚህ ባለፈም ህገ-ወጥ የነዳጅ ግብይትን ለመቆጣጠር የክልሉ የጸጥታ ተቋማት ከፌዴራል ፖሊስና ከጉምሩክ ኮሚሽን ጋር በቅንጅት እየተሠራ ነው ብለዋል።
በዚህም ህገ-ወጥ የነዳጅ ዝውውርን ለመግታት በተደረገው ጥረት 3ሺህ 500 ሊትር ነዳጅ ከሰሞኑ በቁጥጥር ስር መዋሉን ገልጸዋል።
ህብረተሰቡ ህገ-ወጥ የነዳጅ ዝውውርን ለመቆጣጠር በሚደረገው ቅንጅታዊ ስራ ያለውን ተሳትፎ እንዲያጠናክርም ሃላፊው ጠይቀዋል።
በክልሉ አዲሱ የነዳጅ ጭማሪ ታሪፍ መደረጉንና ህብረተሰቡ ነዳጅን በቁጠባ እንዲጠቀም የግንዛቤ ስራ እየተካሄደ መሆኑንም ጠቁመዋል።
ህብረተሰቡ ሌሎች ታዳሽ ሀይልን በመጠቀምና አላስፈላጊ ጉዞ በመቀነስ የነዳጅ ቁጠባውን ተግባራዊ እንዲያደርግም መክረዋል።
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 17/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የውጭ ቀጥታ ንግድና ኢንቨስትመንት ስኬት የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ተግባራዊ ውጤት ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ...
Mar 27, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የብዝኅ ኢኮኖሚ ልማት የግሉን ዘርፍ ተሳትፎ በማሳደግ አህጉራዊ የኢንቨስትመንት ማዕከልነትን እያረጋገጠ ...
Mar 26, 2026
አዲስ አበባ፤ የካቲት 21/2017(ኢዜአ)፡- የምግብ ዋስትና እና ሉዓላዊነትን ማረጋገጥ ለነገ የሚተው የምርጫ ጉዳይ ባለመሆኑ በልዩ ትኩረት መረባረብ እንደሚገባ...
Feb 28, 2025
ሐረር፤ የካቲት 16/2017(ኢዜአ)፦ ባለፉት ዓመታት የተከናወኑ ሁሉን አቀፍ ስራዎች የህዝቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አ...
Feb 24, 2025